
Sunday, May 31, 2015
ግለሰቡ በትግራይ ክልል 6 ሰዎችን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ ገደለ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ስላለው ሁለንተናዊ ቀውስ በመወያየት ሁሉን አቀፍ የአማራጭ ኃይል የሚቋቋምበትን ሂደት ለመምከር ከጁላይ 2-3 በዋሽንግተን ዲሲ የሀገር አድን ጉባዔ በጋራ ይዘጋጃል -

ሥርዓቱ ባሳለፍነው ሳምንት ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል አስቀድሞ የታወቀውን የህወሓት/ኢህአዴግ የምርጫ ድራማ በማካሄድ፤ ሕዝብን ተስፋ በማስቆረጥና ግፉን አሜን ብሎ በመቀበል፤ ቀደም ሲል ሲያደረግ የነበረውን ሀገር የማፈራረስ ሂደትና የሕዝብን ስቃይ የሚያበዛ አገር በቀል የአፓርታይድ አገዛዝ ለቀጣይ አምስት አመታት ለማስቀጠል የሚያስችለውን ህጋዊ ሽፋን በማመቻቸት ላይ በሚገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፤ አገር አድን የምክክር ጉባዔ በማድረግ በሕዝብ ተቀባይነትና ታማኝነት ያለው ሁሉን አቀፍ የአማራጭ ኃይል በማቋቋም ትግሉን በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠል ወቅታዊና አስቸኳይ ነው።
ከላይ በመግቢያው ላይ የተዘረዘሩት ድርጅቶች፤ ከተለያዩ አክቲቪስቶችና ታወቂ ግለሰቦች ጋር በመሆን ከጁላይ 2-3 የምክከር ጉባዔ በጋራ ያዘጋጃሉ። የጉባዔውን ውጤት ለማሳወቅ ሕዝባዊ ስብሰባም ይዘጋጃል። የመሰብሰቢያ ቦታ፤ ዝርዝር ፕሮግራሞችና ተያያዥ እንቅስቃሴዎችን በተከታታይ እንደምናሳወቅ ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን።
ስለዚህ፤ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የፓለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ መኅበራት፣ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆናችሁ ወጣቶች፤ በሀገራችን ነፃነት ሠላም እኩልነትና ፍትኅ ይሰፍን ዘንድ የምትተጉ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ አዘጋጆች፣ የፓልቶክ ክፍሎች፣ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የእምነት አባቶች፤ እንዲሁም ለሀገር ደህንነት ተቆርቋሪ የሆናችሁ ዜጐች በሙሉ፤ የሚገነባው የተባበረ አማራጭ ኃይል ባለቤት እንደመሆናችሁ መጠን የሂደቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን፤ በሀገራችን ነፃነት እውን እንዲሆን በሚደረገው ወሳኝ ሕዝባዊ ትግል ውስጥ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ ታበረክቱ ዘንድ፤ እንዲሁም በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርጉ አደራ እያልን በአክብሮት ሀገራዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ይህ አደገኛ የቁልቁለት ጉዞ እንዲገታ በጋራ እንቁም!
የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (SHENGO)
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት (ENTC)
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ህብረት (UEM-PMSG)
የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ (EYNM)
ግንቦት 22፤ 2007 (May 30, 2015)
የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ የሃያ ዘጠነኛ የፍርድ ቤት ውሎ – ዞን9

የፍርድ ቤቱ ብይን
ፍርድ ቤቱ በ29ኛ ቀጠሮው ተጨማሪ ምስክሮችን ለመስማት እና ሲዲ ማስረጃዎች ላይ ብይን ለመስጠት የነበረ ሲሆን በዚህም መሰረት
1. የሲዲ ማስረጃ ተብለው አቃቤ ህግ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ነገር ግን በስተመጨረሻ ከኮምፒውተር ላይ የሰነድ ማስረጃዎቸን ለመገልበጥ ብቻ የተጠቀምኩባቸው ናቸው ያላቸውን ሲዲዎች የኤግዚቢትም የሰነድም ማስረጃ ስላልሆኑ ሙሉ ለሙሉ አንዲሰረዙ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡ አቃቤ ህግ ከመጀመሪያው የማስረጃ መስማት ሂደት አንስቶ እስከ 28ተኛው ቀጠሮ ድረስ አንዴ ባለሞያዎች የሉም ሌላ ጊዜ የወንጀሉ ኤግዚቢት ናቸው ሲላቸው የከረሙትን ሲዲዎች በስተመጨረሻ ምንም አይነት የተለየ ይዘት ያላቸው ሲዲዎች የሉኝም ሲል አምኗል፡፡ እነዚህ ሲዲዎችን አስመልክቶ ብቻ ትንሽ የማይባሉ ቀጠሮዎች መሰጠታቸው ከዚያም በተጨማሪ የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ እነዲሁም የጠበቆች እና የፍርድ ቤቱ ጊዜ እና ጉልበት መባከኑ ይታወቃል፡፡
ፍርድ ቤቱ በ29ኛ ቀጠሮው ተጨማሪ ምስክሮችን ለመስማት እና ሲዲ ማስረጃዎች ላይ ብይን ለመስጠት የነበረ ሲሆን በዚህም መሰረት
1. የሲዲ ማስረጃ ተብለው አቃቤ ህግ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ነገር ግን በስተመጨረሻ ከኮምፒውተር ላይ የሰነድ ማስረጃዎቸን ለመገልበጥ ብቻ የተጠቀምኩባቸው ናቸው ያላቸውን ሲዲዎች የኤግዚቢትም የሰነድም ማስረጃ ስላልሆኑ ሙሉ ለሙሉ አንዲሰረዙ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡ አቃቤ ህግ ከመጀመሪያው የማስረጃ መስማት ሂደት አንስቶ እስከ 28ተኛው ቀጠሮ ድረስ አንዴ ባለሞያዎች የሉም ሌላ ጊዜ የወንጀሉ ኤግዚቢት ናቸው ሲላቸው የከረሙትን ሲዲዎች በስተመጨረሻ ምንም አይነት የተለየ ይዘት ያላቸው ሲዲዎች የሉኝም ሲል አምኗል፡፡ እነዚህ ሲዲዎችን አስመልክቶ ብቻ ትንሽ የማይባሉ ቀጠሮዎች መሰጠታቸው ከዚያም በተጨማሪ የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ እነዲሁም የጠበቆች እና የፍርድ ቤቱ ጊዜ እና ጉልበት መባከኑ ይታወቃል፡፡
2. አቃቤ ህግ የጠየቀውን ተጨማሪ ምስክሮች ተፈልገው አንዲመጡ ጊዜ ይሰጠኝ ያለውን ጥያቄ አስመልክቶ ምስክሮቹ አሁንም የደረጃ ምስክሮች በመሆናቸው እቃ ሲፈተሽ አይተናል ከማለት ውጪ ስለማይመሰክሩ አቃቤ ህግም በተደጋጋሚ በፍርድ ቤቱ እድል ተሰጥቶት ምንም የተለየ ምስክር ሊያቀርብ ባለመቻሉ ተጨማሪ ምስክሮችን ለማቅረብ ተጨማሪ ቀጠሮ አይሰጠውም በማለት የምስክሮቹን ጉዳይ ፍርድ ቤቱ ዘግቶታል፡፡
አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስን የተመለከተ ማስረጃ
አቃቤ ህግ እስካሁን ምንም ሳይል የቆየባት አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስን በተመለከተ በትናንትናው የፍርድ ቤት ውሎ ማጠቃለያ ላይ አንድ ዶክሜንተሪ የያዘ ሲ.ዲ በማስረጃነት ማቅረቡን ገልጾ ፍርድ ቤቱ እንዲመለከተው ማመልከቱ ይታወሳል፡፡ ይህን የሲ.ዲ ማስረጃ በተመለከተ በ29ኛው ችሎት ቀጠሮ ብይን የተሰጠ ሲሆን፣ በብይኑ መሰረትም ትላንትና ከሰዓት በኋላ አቃቤ ህግ ሲ.ዲውን በጽ/ቤት በኩል እንዲያስገባ ታዝዟል፡፡ ፍርድ ቤቱ ጨምሮ እንደገለጸው በአንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን ዶክሜንተሪ በቢሮ ዳኞቹ እንዲመለከቱት ከተደረገ በኋላ ሲ.ዲው ሌሎችን ተከሳሾች ይመለከታል ወይስ አይመለከትም የሚለውን አይቶ ብይን የሚሰጥ ይሆናል፤ ብይኑን ለመስጠትም ለሰኔ 8/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ሲ.ዲው የያዘው ዶክሜንተሪ በግልጽ ቢታይ የሚያስከትለው ጉዳት አለ ወይስ የለም የሚለውንም ፍርድ ቤቱ ብይን እንደሚሰጥበት ይጠበቃል፡፡ አቃቤ ህግ በቀደመው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ አመጽ ስታነሳሳ የሚያሳይ ዶክመንተሪ ሲዲ አለኝ ማለቱ ይታወሳል፡፡
አቃቤ ሀግ ጠበቆች ላይ ያቀረበው አቤቱታ
አቃቤ ህግ በዚሁ ችሎት ጠበቆች የፍርድ ቤቱን ውሎ አስመልክቶ የሚሰጡትን አስተያየት የአንድ ወገን አስተያት ከመሆኑም በላይ የፍርድ ሂደቱን ተጽእኖ ሊያመጣ ይችላል የሚል በቤቱታ አቅርቧል፡፡
አቃቤ ህግ በዚሁ ችሎት ጠበቆች የፍርድ ቤቱን ውሎ አስመልክቶ የሚሰጡትን አስተያየት የአንድ ወገን አስተያት ከመሆኑም በላይ የፍርድ ሂደቱን ተጽእኖ ሊያመጣ ይችላል የሚል በቤቱታ አቅርቧል፡፡
ጠበቃ አምሃ መኮንን በበኩላቸው አቃቤ ሀግ እዚህ አንድ ተከራካሪ ወገን አንጂ የሂደቱ አዛዥ አለመሆኑን በተጨማሪም ግድፈት ካለ የተጣሰውን ህግ ግድፈት በጽሁፍ አቤቱታ ማቅረብ አንደሚችል ከዚያ ውጪ ግን በግልጽ የተሰየመውን ችሎት ከአገር ቤት እስከአለም አቀፍ ሚዲያዎች በዝርዝር አንደሚዘግቡትና የጠበቃው አስተያየትም ከዚህ የተለየ አንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ‹‹የተሰጠው አስተያየት አቃቤ ህግ በሰጠው ቃል መሰረት ተፈጽሞ ከሆነ ስህተት ስለሆነ ሊስተካከል ይገባል›› በሚል ማሳሰቢያ ብቻ አልፎታል፡፡
በፍርድ ቤትም ውስጥ የታፈነው የተከሳሾቹ ድምጽ
ብይኑ መሰማት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተደጋጋሚ ጥያቄ ለመጠየቅ ሲጠይቁ የነበሩት ተከሳሾች በፍርድ ቤቱ እድል አልተጣቸውም ፡፡ በተለይም የአቶ አመሃን የሚዲያ አስተያት ተከትሎ
ብይኑ መሰማት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተደጋጋሚ ጥያቄ ለመጠየቅ ሲጠይቁ የነበሩት ተከሳሾች በፍርድ ቤቱ እድል አልተጣቸውም ፡፡ በተለይም የአቶ አመሃን የሚዲያ አስተያት ተከትሎ
ጦማሪ ናትናኤል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሳይቀር በተከሳሾች ላይ የወንጀለኛነት ንግግር ሲያደርጉ መደመጣቸውን በማስታወስ የፍርድ ቤቱ ማሳሰቢያ ለእሳቸውም ይሁን በማለት ንግግሩን ለማብራራት ሲሞክር ፍርድ ቤቱ ‹‹ይሄ የአቶ አምሃ ጉዳይ እንጂ እናንተን አያገባችሁም›› በሚል አቋርጦታል፡፡ ጦማሪ ዘላለም ክብረትም አንዲሁም ጋዜጠኛ አስማመው ሃይለጊዬርጊስ በተመሳሳይ ሀሳቡን ለመግለጽ ጠይቀው ተከልክለዋል፡፡ ጦማሪ ናትናኤል ፍርድ ቤቱ ሳይፈቅድለት ተናግሯል ወደጎንም ዞሮ አውርቷል በማለት ፍርድ ቤቱ ለጥያቄ አንዲነሳ ሲታዘዝ የናትናኤል ጥያቄ የሁላችንም ጥያቄ ነው በማለት ሁሉም ተከሰሶች አብረውት ተነስተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ሎሎቹ ተከሳሾ አንዲቀመጡ ቢያሳስብም አንቀመጥም በማለት አብረውት ቆመዋል፡፡
ናትናኤል መናገር ሲከለከል ‹‹ከአሁን በፊትም ሀሳባችን እንዳንገልጽ ገደብ ባደረጉብን ዳኛ ላይ አቤቱታ ማሰማታችን ይታወሳል፡፡ ህገ መንገስታዊ መብታችንን አክብሩ…ሀሳባችንን እንግለጽ›› ሲል ተናግሯል፡፡ ፍርድ ቤቱ ግን ንግግሩን አስቁሞ በመሐል ዳኛው አማካኝነት ‹‹ወዳልሆነ ነገር አታስገቡን›› ሲል ዛቻ መሰል ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡
በዚህ ያላበቃው የተከሳሾችና የፍርድ ቤቱ ውዝግብ ጦማሪ አቤል አሁንም ለመናገር አድሉ አንዲሰየው ሲጠይቅ ” ስነስርአት ያዙ ” በማለት ፍርድ ቤቱ በመከልከሉ ጦማሪ አቤል ” እኛ ብቻ ሳንሆን ራሳችሁም ስነስርአት አድርጉ ጥያቄ አለን ሰምታችሁ ምላሽ ስጡን” በማለት ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ይህንን ምላሹን ፍርድ ቤቱ ችሎት መድፈር ነው ብሎታል፡፡ ይህንን ተከትሎ ጠበቆች ጣልቃ በመግባት ደንበኞቻቸው አንዲደመጡ ፍርድ ቤቱን በማሳሰብ አቤልም ይህን እድል በመነፈጉ በስሜታዊነት የተናገረው በመሆኑ በተግሳጽ አንዲታለፍ ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ አቤልን በዚህ የጠበቃው ሃሳብ ይስማማ እነደሆነ ሲጠየቅ የጠየቁት መብቴን ነው የምጠይቀው ይቅርታ የለም በማለቱ የችሎት መድፈሩን አስመልክቶ ውሳኔ ለመስጠት ለግንቦት 25 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ይህንን ተከትሎ የአቤል ሀሳብ የሁላችንም ሃሳብ ስለሆነ ሁላችነም በዚያ ቀን ልንቀርብ ይገባል የሚል አቤቱታ ሁሉም ተከሳሾች ቢያሰሙም ፍርድ ቤቱ ፓሊስን አንዲያስወጣቸው በመታዘዙ ችሎቱ ወጥተዋል፡፡ በኋላ ከተከሳሾች ጠበቆች አንደገለጹት የጦማሪ አቤል ጥያቄ አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ የሚቀርበው የተባለውን የዶክመንተሪ ማስረጃ ሎሎች ተከሳሾችም አንዲያዩት ለመጠየቅ ነበር ፡፡
የዞን 9 ማስታወሻ
1. ዘግይቶም ቢሆን የተወሰደውን የፍርድ ቤቱን የሲዲ ማስረጃዎቸን መሰረዝ አንዲሁም ለአቃቤ ህግ ተጨማሪ ጊዜ አለመስጠት ውሳኔ እናበረታታለን ፡፡ ይህ ውሳኔ ከሶስት ቀጠሮ አስቀድሞ መወሰድና የጓደኞቻችን የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት ሊከበር ቢገባውም አሁንም ቢሆን ከመቅረት ይሻላል ፡፡ ፍርድ ቤቱም ይህንን መሳይ ፈጣን ምላሾችን በመስጠት ጓደኞቻችን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ማሰናበት የሚቀጥለው ብይን ሊሆን ይገባል፡፡ ያልተሰራ ወንጀል ምስክርም ሆነ ማስረጃ ለአመታት ቢፈለግም አይገኝለትም ፡፡
2. ፍርድ ቤት ውስጥ ያለውን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አሁንም አሳሳቢ ነው ፡፡ ተከሳሾች ሃሳባቸውን አንዲሰጡ መፍቀድ አንድ ገለልተኛ ፍርድ ቤት ለተከሳሾች ሊሰጠው የሚገባ መሰረታዊ መብት ሆኖ ሳለ ተከሳሾች ይህንን መብት በተደጋጋሚ መነፈጋቸው ከዚም አልፎ ይህንን መብት በመጠየቃቸው ችሎትን አንደደፈሩ መቆጠሩ በጣም አሳዛኝ ነው፡። የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እንኳን አሁን ታስረንና ተሰደን መስዋእትነት እየከፈልንበት እያሉ ቀርቶ ቀድሞም ሃሳብን የነጻነት የመግለጽ መብት የማይቀየር ቋሚ እሴታችን አንደሆነ ይታወቃል፡፡ ፍርድ ቤቶች ይህንን ቀላል መብት መንፈጋቸው ደግሞ የተለመደውን የስራ አስፈጻሚው አካልነታቸው ሃሜት የሚያጠናክር ከመሆን ውጪ ሌላ ፋይዳ የለውም ፡፡
አሁንም ስለሚያገባን እንጦምራለን
ዞን9
ዞን9
ከገዢዎቻችን ለምን አንማርም ? – ግርማ ካሳ

የሚከተለው ኢሳት ከዘገበው የተወስደ ነው። ዜናውን ለመቀበል አላዳገተኝም። “የሰላም በር ሲዘጋ የአመጽ በር ይከፋታል” እንዳለው አብርሃ ደስታ፣ ፍጹም አሳፋሪ የሆነው የምርጫው ሂደትና የምርጫው ዉጤት፣ ብዙ ዜጎች ሰላማዊዉን እና ሕጋዊዉን መንገድ ትተው ሌላ የትግል አማራጭ እንዲከትሉ ነው የገፋፋቸውና የሚገፋፋቸው።
ሆኖም አንድ ነገር ጠንቅቀን ማወቅ አለብን። መለስ ዜናዊ የሞተ ጊዜ ተከፋፈሉ ወዘተረፈ እያልን ስናወራ ነበር። ግምገማ ተደራረጉ ብለንም ስለነርሱ ስንተነትን ጊዜ አጠፋን። ምናልባት እነርሱ እርስ በርስ ከተከፋፈሉ በግርግር ለዉጥ ይመጣል ከሚል ተስፋ።
ሰዎቹ እርስ በርስ ይጠማመዱ ይሆናል። ነገር ግን መቼም አይለያዩም። ያውቃሉ፣ አንዱ ከወደቀ ሌላዉም እንደሚውድቅ። እነ አባዱላ ፣ እነ አዲሱ ለገሰ፣ እነ ሬድዋን ሁሴን ፣ ሕወሃት ከሌለ የነርሱ እጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ይዉቃሉ። ስለዚህ አንዱ በአንዱ ላይ እንደ መዥገር ተጣብቆ ነው የሚጓዙት። ሥር የሰደደም ልዩነት ቢኖራቸውም፣ ተያይዘው ፣ ጀርባ ለጀርባ እየተታከኩ የግፍ አገዛዙን ይቀጥላሉ።
በነርሱ መካከል እርስ በርስ ልዩነቶች ተፈጥረው፣ ሞደሬት የሆኑት አይለው ቢወጡና አገር መረጋጋት ብትችል ደስ ነው የሚለኝ። ግን የሚሆን ነገር አይደለም። እነርሱ አይለያዩም። አንድ ናቸው።
በተቃራኒው እኛ ግን ትናንሽ ልዩነቶች እያለያዩን በጋራ መንቀሳቀስ አልቻልንም። በአገር ቤት ሰማያዊ፣ አንድነት፣ መኢአድ ፣ ትብብር …እንዲሁም ሌሎች ለምን በአንድ ላይ መስራት አልቻሉም ? መድረኮች ከነሰማያዊ ጋር ለምን መስራት አልቻሉም ? ወደ ዉጭ አገር ስንመጣ ደግሞ ሸንጎ፣ የሽግግር ምክር ቤቱ፣ ግንቦት ሰባት፣ ሶሊዳሪቲ ….ለምን አብረው ፣ አንድ አማራጭ ኃይል አቋቁመው መስራት አልቻሉም? ሁሉም ነጻነት ፈላጊ አይደሉም እንዴ ? ሁሉም ፍትህና ዴሞክራሲን ናፋቂ አይደሉም እንዴ ? ሁሉም ለአንዲት ኢትዮጵያ የቆሙ አይደሉም እንዴ ? ታዲያ ለምን መተባብር ቸገራቸው ?
ወገኖቼ, ደግሜ እላለሁ ገዢዎቻችን አይለያዩም። እነርሱ አንድ ሆነው፣ እኛ ደግሞ ተለያይተን እስከቀጠልን ድረስ ረግጠው፣ አዋርደው ይገዙናል። አራት ነጥብ። በተናጥል በባዶ፣ እንጮሃለን፣ እንኮንናችቸዋለን፣ ዘራፍ እንላለን ፣ የመግለጫ ዉርዥብኝ እናወርዳለን ። ግን የምናመጣው ነገር አይኖርም።
ስለዚህ ለዉጥ ክአገዛዙ ከራሱ ቢመጣ እስየው። ስንማጸንና ስንጎተጎት የነበረ ስለሆነ። ሆኖም ከአሁን በላይ ተስፋን እነርሱ ላይ ሳይሆን፣ አምላካችን እና አምላክ በሰጠን የተባበረው ክንዳችን ላይ መሆን ነው ያለበት። እመኑኝ ስርዓትቱ የበሰበሰ ስርዓት ነው። ገና ድሮ መወገድ የሚችል ስርዓት ነበረ። እስከ አሁን የቆየው እኛ ስለፈቀድንለት ብቻ ነው። አሁንም በአንድነት መንቀሳቀስ ካልቻልን፣ በአፋችን ብንናገረዉም ስርዓቱ እንዲቀጥል እየፈቀድንለት ነው።
ገዢዎቻችን ለክፋት አንድ ከሆኑ፣ እኛ ለመልካም ነገር እንድ መሆን እንዴት ያቅተናል ?
ገዢዎቻችን ለክፋት አንድ ከሆኑ፣ እኛ ለመልካም ነገር እንድ መሆን እንዴት ያቅተናል ?
በሃመር ወረዳ ከፍተኛ እልቂት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ

ነጻነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው!!!

በእነዚህና በሌሎችም ህገ ወጥ አሰራሮች ታጅቦ የተካሔደው ምርጫ በምንም መመዘኛ ፍትሃዊ፣ ነፃና ተአማኒ ሊሆን እንደማይችል ሒደቱ በግልፅ አመላካች ነው፡፡ በውጤቱም በሐገራችን የዲሞክራሲና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት መኖርን ወደ መቃብር የከተተና ኢትዮጵያ የአንድ ፓርቲ ስርዓት ሐገር መሆኗን ያረጋገጠ በውጤቱም የገዥውን ቡድን 100% አሸናፊነት አከናንቦታል፡፡ ይህ ውጤት ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ የጨለማ ዘመን መምጣቱን ከማሳየቱ ባሻገር ኢህአዲግ በፍርሃት ተውጦ ሁሉንም ለመቆጣጠር ባደረገው ሩጫ ለመግለፅ እስኪያፍር ድረስ የሚያሸማቅቅ ውጤት እንዲከናነብ ሆኗል፡፡
በርካታ ኢትዮጵያውያን በምርጫው ሂደት ተስፋ በማጣት የመራጭነት ካርድ እንዳልወሰዱ የታወቀ ቢሆንም በአፈና ስርዓቱ ኢህአዲግን እንዲመርጡ በከፍተኛ ጫና የመራጭነት ካርድ የወሰዱ ዜጎች ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸውን የፖሊሲ አማራጮችና ለሐገራችን ያለውን ቀናኢ አመለካከት በመገንዘብ ሳይገደዱ፣ በጥቅም ሳይታለሉ ወይም ሌላ ማንኛውንም ስጦታ ሳይጠብቁ ለሰማያዊ ፓርቲ የሰጡት ድምፅ እጅግ የሚያስደምም ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ፓርቲያችን በዚህ አፈናና ጭቆና ውስጥ ከሕዝብ የተሰጠውን ክብርም ያከብራል፣ ያመሰግናል፡፡ በምርጫ ሂደቱ የተደበደባችሁ፣ የተሳደዳችሁ፣ የታሰራችሁ እና የተንገላታችሁ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲያችን ዛሬ በኢትዮጵያ ሕዝብ ተዓማኒ፣ ተወዳጅና ተስፋ የተጣለበት እንዲሆን እናንተ ላይ የደረሰው መከራና በደል ትልቁን ድርሻ ይወስዳልና ክብርና ምስጋና ይገባችኋል፡፡
በመጨረሻም ከላይ በተዘረዘሩት ሕገወጥና የአፈና ስርዓት የተካሔደው የ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫ የሚያመላክተው ኢትዮጵያ አሁንም ነፃና ፍትኃዊ ምርጫ ልታካሂድ ቀርቶ በኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከተካሔዱት ምርጫዎች ጋር እንኳ ሊወዳደር የማይችል እጅግ ኢፍትኃዊ፣ ወገንተኛና ተዓማኒነት የሌለው በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ ሂደቱንም ሆነ ውጤቱን አይቀበለውም፡፡ በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስትም በሕዝብ ተቀባይነት የለውም፡፡ የዜጎች ነፃነት ሳይከበር ነጻና ፍትኃዊ ምርጫ ሊደረግ ስለማይችል አሁንም ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻችን እስከሚከበሩ ድረስ ሰማያዊ ፓርቲ በሚያካሂደው የነጻነት ትግል ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ እየጠየቀ ለነፃነት የሚደረገው ትግል ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያሳውቃል፡፡
ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም
አዲስ አበባ
አዲስ አበባ

Thursday, May 28, 2015
የዛሬ 24 ዓመት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ባይቆጣጠር ኖሮ ዛሬ የኢትዮያ እድገት ከብራዚል ጋር ይስተካከል ነበር 28 (የጉዳያችን ማስታወሻ) -

ግንቦትና ግንቦታውያን

ምርጫ ቦርድ የአስቂኙን ምርጫ ውጤት ይፋ አደረገ * ኢሕአዴግ 100% አሸነፈ አለ * ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ወንበር አላገኘም -

የሳምንቱ ማስታወሻ – ኤርሚያስ ለገሰ

የዞን 9 ጦማርያን የዛሬ የፍርድ ቤት ውሎ

በዚህ መሰረት አቃቤ ህግ በኤግዚቢትነት የያዛቸውን ላፕቶፕ፣ ሞባይል፣ ሲምካርድ፣ ሃርድ ዲስክ ይዞ ቀርቧል፡፡ ሆኖም ግን ሲ.ዲዎችን በተመለከተ ሲጠየቅ ‹‹ሲ.ዲዎቹ እየመጡ ነው››የሚል ምላሽ በመስጠቱ እና የተከሳሾች ጠበቆች ሲዲዎቹ ሳይመጡ ምስክሮች መሰማት የለባቸውም ብለው በመቃወማቸው ሲዲው ከማእከላዊ ምርመራ እስኪመጣ ምስክሮች አያሰሙም ተብሎ ለከሰአት ተቀጥሮ ነበር ፡፡
ከሰአት በኋላ አቃቤ ህግ ቀሪ ናቸው ካላቸው 16 ምስክሮች መካክል 3ቱን ብቻ ይዞ የቀረበ ሲሆን 13ቱን ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል፡፡ የቀረቡት ሶስቱንም ፍተሻ ሲከናወን ያዩ የደረጃ ምስክሮች ሲሆኑ ፍተሻ ሲከናወን ከማየታቸው በስተቀር ተጨማሪ ነገር መመስከር አልቻሉም ፡፡
የምስክሮች ቃል

ለምስክሩ ‹‹ሲ.ዲው ባዶ ይሁን የተጻፈበት ይሁን ያየኸው ነገር ነበር›› የሚል መስቀለኛ ጥያቄ ሲቀርብለት ‹‹አላየሁም›› ሲል መልሷል፡፡ ሲ.ዲው ላይ ፈርመሃል ሲባልም መፈረሙን አስረድቷል፡፡ በዚህ ጊዜ የፈረመበትን ሲ.ዲ እንዲያሳይ ተጠይቆ አቃቤ ህግ ጣልቃ በመግባት ‹‹ኤዶም ላይ ሲ.ዲ በማስረጃነት አልያዝንም›› የሚል አስገራሚ መልስ ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ ምስክሩ 30 ገጽ የእንግሊዝኛ ጽሁፍ የተጻፈበት ወረቀት ላይ መፈረሙን ስለገለጸ ፊርማውን እንዲለይ ሰነዱ ይቅረብላቸው ሲባልም አቃቤ ህግ ‹‹በማስረጃነት አላያያዝንም›› ብሏል፡፡ ምስክሩ ሁለት በማስረጃነት ባልተያዙ ሰነዶች ላይ ነበር ምስክርነቱን የሰጠው ፡፡ በተጨማሪም በፍተሻ ወቅት የተገኘውን ላፕቶፕ እነዲያሳይ የተጠየቀው ምስከሩ የጦማሪ አቤል ዋበላን ላፕቶፕ አሳይተዋል፡፡
20ኛ ምስክር፡- እኒህ ምስክር ደግሞ ቢላል ሙሄ የሱፍ የሚባሉ ሲሆን 38 አመታቸው ነው፡፡ ‹‹ሚያዝያ 2006 ፌደራል ፖሊስ የተስፋለምን ቤት ሲፈትሽ በታዛቢነት አይቻለሁ፡፡ ቤቱን የከፈተው ተስፋለም ነው፡፡ ቤቱ ውስጥ ብዙ መጽሔትና ጋዜጦች፣ መጽሐፎች፣ ወረቀቶች፣ መቅረጸ ድምጽ፣ ላፕቶፕ ተገኝተዋል፡፡›› ተስፋለም ቤት 28 ሲዲዎች ተገኝተዋል ያሉት ምስክሩ ምን አይነት ይዘት አንደነበራቸው ባዶ ይሁኑ ጽሁፍ ያላቸው አላውቅም እነዲሁም ሲዲዎቹ ወጥቶ የታተመ ነገር አላስታውስም ብለዋል፡፡
21ኛ ምስክር፡- ሚሊዮን አሸብር ደግሞ የ31 አመት በንግድ ስራ ላይ የተሰማራ የአ.አ ነዋሪ ነው፡፡ ለምስክርነት መምጣቱን የገለጸው ሚሊዮን በማን ላይ ልትመሰክር ነው የመጣኸው ሲባል በአማኑኤል ፈለቀ ላይ ሲል መልሷል፡፡ ሆኖም ግን ዳኞች ደጋግመው ሲጠይቁት ስሙን አስተካክሎ በናትናኤል ፈለቀ ላይ ሊመሰክር መሆኑን ገልጹዋል፡፡
‹‹ሚያዝያ 17/2006 ቂርቆስ ክ/ከተማ ኮንስትራክሽን ባንክ ፌደራል ፖሊስ የፍርድ ቤት ወረቀት አሳይቶ ፍተሻ ሊያደርግ ስለሆነ እንድታዘብለት ጠይቆኝ ታዝቤያለሁ፡፡ ናትናኤል ፍተሻው እንዲካሄድ ፈቃደኛ ነበር፡፡ በዚህ መሰረት ተፈትሹዋል፤ ፍተሻውንም አይቻለሁ፡፡ ላፕቶፕ፣ ሲ.ዲዎች (በቁጥር ወደ 16 የሚሆኑ) እና ሰነዶች ተገኝተዋል፡፡ የተገኙት ነገሮች ላይ ፈርሜያለሁ ፡፡ ሲዲም ሆነ ላፕቶፑ ውስጥ ያለውን ነገር ይዘት አላየሁም አላውቅምም ብሏል ፡፡ ላፕቶፑንም ቀርቦ አሳይቷል ፡፡
ሲዲዎቹ
አወዛጋቢዎቹ ሲዲዎች ዛሬም ቀርበዋል ተባለ እነጂ በአቃቤ ህግና በጠበቆች መካከል ያለው ክርክር አልተቋጨም ፡፡ ሲዲዎቹ ኤግዚቢት ስለሆኑ ለተከሳሾች ለማድረስ አልገደድም ሲል የነበረው የአቃቤ ህግ ክርክር ዛሬ ሲዲዎቹ የሰነድ ማስረጃው ላይ የተያያዙትን ሰነዶች ከላፕቶፕ የገለበጥንባቸው ናቸው ብሎ የሰነድ ማስረጃ አካል አድርጓቸዋል ፡፡ የተከሳሽ ጠበቆች ሲዲዎቹ ማስረጃ ከሆኑ ሊሰጠን ይገባል ሲሉ አመልክተዋል፡፡ ሲዲዎቹ አንድ ወይም ሁለቱ ናቸው የቪዲዮ ማስረጃ ያላቸው ሌላው ከክሱ ጋር የተያያዘውን ሰነድ የገለበጥንበት ነው፣ ሁሉም በሰነድ የተያየዙ ናቸው ሲል አቃቤ ህግ አዲስ የህግ ፍሬ ነገር አቅርቧል፡፡
የአንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበ ማስረጃ
አቃቤ ህግ በዛሬው ውሎው አዲስ ግኝት ይዞ መጥቷል፡፡ የሲዲ ውዝግቡ መሃል ላይ “አንድ ዶክምንተሪ አንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበና ቡድኑ ለቅስቀሳ ይጠቀምበት የነበረ አለንና ፍርድ ቤቱ ሌሎች ማስረጃዎችን አቅርበን ሰንጨርስ ይሄንን ሲዲ እንዲያይልን” ብሏል፡፡ አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ በማስረጃነት አለኝ ያለው ሲዲ መቼ የተገኘ አንደሆነ ምን ይዘት እንዳለው የተጠቀሰ ነገር የለም ፡፡
በመጨረሻም አቃቤ ህግ ቀሪ 13 የደረጃ ምስክሮቹን ፈልጎ ለማቅረብ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ ብሏል፡፡ የተከሳሽ ጠበቆችም ሲዲዎቹ የሰነድ ማስረጃዎች ከሆኑ እንዲሰጣቸው ካልሆነም ኢግዚቢትነታቸው ምዝገባ እንዲለይ ጠይቀዋል፡፡ በሁለቱ ጉዳዬች ላይ ለመወሰን ለነገ ጠዋት ግንቦት19 ከጠዋቱ 3 ሰአት ተቀጥሯል፡፡
የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች በከፍተኛ የአካልና የመንፈስ ደህንነት ሆነው የታዬ ሲሆን ቀኑን ሙሉ ፍርድ ቤት ጊቢ ውስጥ አብረው ለመዋል እድል አግኝተዋል፡፡
የዞን ማስታወሻ
ከዚህ በፌት በተደጋጋሚ አንደጠቀስነው ያልተሰራ ወንጀል ማስረጃና ምስክር አይገኝለትምና ተከሰሾችን መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ በማሰናበት ፍርድ ቤቱ ሃላፌነቱን በመወጣት ከህግ የበላይነት ጎን መሆኑን አንዲያሳይ በድጋሚ አንጠይቃለን፡፡
ከዚህ በፌት በተደጋጋሚ አንደጠቀስነው ያልተሰራ ወንጀል ማስረጃና ምስክር አይገኝለትምና ተከሰሾችን መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ በማሰናበት ፍርድ ቤቱ ሃላፌነቱን በመወጣት ከህግ የበላይነት ጎን መሆኑን አንዲያሳይ በድጋሚ አንጠይቃለን፡፡
የአሜሪካ መንግስት ምርጫውን አሽሟጠጠው::

ለፍትሃዊ እና ነጻ ምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ነጻ እና ለቅስቀሳ የሚሆን የመረጃ ማሰራጫ ሚዲያ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብቶች ሲቭክ ማህበራት እንዲሁም የተላያዩ አለም አቀፍ እና ሃገር አቀፍ ሕብረተሰቦች በታዛቢነት ባልተወከሉበት ምርጫ ማካሄድ አያስኬድም ሲል መግለጫው አሽሟጧል::ጋዜጠኞችን በማሰር እና በማሳደድ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገደብ በመስጠት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ጣልቃ በመግባት የፖለቲካ ምህዳሮችን በማጥበብ ምርጫ ማካሄድ አይሞከርም ሲል መግለጫው ተናግሯል::
የአሜሪካ መንግስት ከኢትዮጵያ እና ከሕዝቧጋር ጠንካራ ግንኙነት አለው ያለው መግለጫው ዲሞክራቲክ ተቋማት ዕንዲጠናከሩ የፕሬስ ነጻነተ እንዲያብብ በሃገሪቱ የታፈነው የፖለቲካ ምህዳር ሁሉ ክፍት እንዲሆኑ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአለም አቀፍ ሰባዊ መብቶች ድንጋጌ ግዴታዎች እንድታከብር አብረን እንሰራለን ብሏል::
መድረክ ባለፈው እሁድ የተካሄደውን አምስተኛው አገር አቀፍ አጠቃላይ ምርጫ ውጤትን እንደማይቀበል ገለፀ -

ምርጫ ቦርድ በዛሬው እለት ያወጣው ጊዜያዊ ውጤት ተቀባይነት የለውም ሲሉ የመድረክ ፓርቲ አመራር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለቢቢኤን ገለጹ
ቢቢኤን ዜና
ምርጫ ቦርዱ በዛሬው እለት ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት መግለጫ ኢህአዴግ 100 ፐርሰንት በደረሱ ጊዜያዊ ውጤቶች ማሸነፉን ገልጽዋል፡፡ ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ያለው መድረክ በበኩሉ በዛሬው እለት በሰጠው አስቸኳይ መግለጫ ይህንን እንደማይቀበለውና በምርጫው ጊዜ የደረሱትን ችግሮች በመዘርዘር ለሁለት ሰአታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የመድረኩ አመራር የሆኑትን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ቢቢኤን አግኝቶ ያነጋገራቸው ሲሆን ከርሳቸው ጋር ያደረገነውን ቆይታ በዛሬው ዝግጅታችን ይጠበቁ
-ቢቢኤን ዜና
ምርጫ ቦርዱ በዛሬው እለት ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት መግለጫ ኢህአዴግ 100 ፐርሰንት በደረሱ ጊዜያዊ ውጤቶች ማሸነፉን ገልጽዋል፡፡ ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ያለው መድረክ በበኩሉ በዛሬው እለት በሰጠው አስቸኳይ መግለጫ ይህንን እንደማይቀበለውና በምርጫው ጊዜ የደረሱትን ችግሮች በመዘርዘር ለሁለት ሰአታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የመድረኩ አመራር የሆኑትን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ቢቢኤን አግኝቶ ያነጋገራቸው ሲሆን ከርሳቸው ጋር ያደረገነውን ቆይታ በዛሬው ዝግጅታችን ይጠበቁ
ምርጫው ተብዬውን ቧልት ላለመታዘብ ወሰንን – አና ጎምሽ

የዘንድሮው ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ተካሄደ፡፡ የምርጫውን ሂደት የታዘበው ብቸኛ ዓለምአቀፍ ተቋም የአፍሪካ ኅብረት ነው፡፡
ለወትሮ የኢትዮጵያን ምርጫዎች ይታዘቡ የነበሩትና አሁንም በዓለም ዙሪያ እየተንቀሣቀሱ የሚታዘቡት የአውሮፓ ሕብረትና የአሜሪካው የካርተር ማዕከል ግን አልተገኙም፡፡ ለምን?
የአውሮፓ ፓርላማ አባል የሆኑትና የ1997ቱ ምርጫ የኅብረቱ የታዛቢዎች መሪ የነበሩት አና ጎምሽ የአውሮፓ ኅብረት ያልታዘበው ምርጫው “ቧልት ስለሆነ ነው” ብለዋል፡፡
“የአውሮፓ ኅብረት የታዛቢዎችን ቡድን በመላክ ለገዥው ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያካሄደ የማስመሰያ ማኅተም መስጠት ስላልፈለግን የደረስንበት የፖለቲካ ውሣኔ ነው” ብለዋል፡፡
ለመሆኑ የኢትዮጵያ መንግሥት አሁን ባለው አቋሙ ዴሞክራሲያዊ፤ ፍትሐዊና ነፃ ምርጫ ለማካሄድ ብቁ ነው?
“አይደለም ብሎ የሚያሣምነኝ እስካልመጣ፤ አዎ ብቁ ነው” ይላሉ በደቡብ ሱዳን የፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ልዩ አማካሪ እንዲሆኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የላካቸው፤ በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የአፍሪካ ስፔሻሊስት ሆነው ለሃያ አራት ዓመታት ያገለገሉት አቶ ቴዎድሮስ ዳኘ፡፡
“ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካ ችግር አለ የሚባል ከሆነ ብዙውን ጊዜውን እርስ በራሣቸው በመጣላትና በውጭ ሃገሮች በመኖር ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ተጠያቂነቱን ሊወስዱ ይገባቸዋል” ብለዋል አቶ ቴዎድሮስ፡፡
Tuesday, May 26, 2015
« በጉልበት ወደ ዘመናዊነት » የጀርመን ታዋቂ ዕለታዊ ጋዜጣ ስለ የኢትዮጵያ ሀገር አቀፋዊ ምርጫ ሲዘግብ

የጀርመን ታዋቂ ዕለታዊ ጋዜጣ « ዙድ ዶይቸ ሳይቱንግ» ስለ የኢትዮጵያ ሀገር አቀፋዊ ምርጫ ሲዘግብ ርዕሱን« በጉልበት ወደ ዘመናዊነት » ነው ያለው። የጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ፓርቲ ኢሀዲግ እንደሚያሸንፍ ጥርጥር የለውም ሲል የዘገበው ይህ ጋዜጣ ፤ «ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በርግጥ ጥሩ የኢኮኖሚ እድገት ያስመዘገበች ሀገር ብትሆንም አሁንም ድረስ እንደ « ልማታዊ አምባገነን» ነው የምትታየው፣ መንግሥት የኤኮኖሚውን አቅጣጫ ብቻ ሳይሆን ህብረተሰቡንም ይቆጣጠራል ሲልም አትቷል ።ጋዜጣው የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶችን ዋቢ በማድረግ፤ ሂስ ሰንዛሪ ጋዜጠኞች በሀገሪቱ ቦታ እንደሌላቸው ወህኒ ቤት የሚገኙ ጋዜጠኞችን እና የኢንተርኔት ዘጋቢዎችን በምሳሌነት ጠቅሶ ያብራራል። ጋዜጣው ስለ ሃገሪቱ ልማትም ፅፏል። ምንም እንኳን ልማቱ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማህበረሰበብ ጋር ባይደርስም፤ በአዲስ አበባ ትላልቅ ፎቆች እየተሰሩ ስለመሆኑና በቅርቡ የቀላል ባቡር አገልግሎት ስራውን እንደሚጀምር ይጠቁማል።
« ዙድ ዶይቸሳይቱንግ»የኢትዮጵያ ምርጫ ሀተታውን ከማጠናቀቁ በፊትም፤ የተቃዋሚዎች እጣ ፋንታ ከባለፈው ምርጫ ጋር ሲነፃፀር አለመሻሻሉንም አንስቷል። እንደ ጋዜጣው ቀውስ ውስጥ ከሚገኙት ከሶማሊያ እና ከደቡብ ሱዳን ጋር ስትነፃፀር ምዕራባውያን ኢትዮጵያን የተረጋጋች ደሴት አድርገው ስለሚመለከቷት የዲሞክራሲ ርዕስ ሲነሳ ፤ ጆሮ ደባ ልበስ ብለው ያልፉታል።
ሌላው ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የዘገበው «ታገስሻው» የተባለው የጀርመን የዜና ማሰራጫ ነው። «ተቃዋሚ ድምፅ የለውም» በሚለው ርዕሱ፤ የምርጫው አሸናፊ ፓርቲ ኢሀአዲግ እንደሚሆን እንደማያጠራጥር ያትታል። ታገስሻው ከዚህም በተጨማሪ ፤ በቴሌቪዥን ሥርጭቱ እና በድረ ገጹ ከሀገር ሸሽቶ ናይሮቢ ውስጥ ጥገኝነት ስለጠየቀው ጋዜጠኛ የትነበርክ እና ደረሰብኝ ስለሚለው በደል ዘግቧል።
ሌላው ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ የዘገበው «ታገስሻው» የተባለው የጀርመን የዜና ማሰራጫ ነው። «ተቃዋሚ ድምፅ የለውም» በሚለው ርዕሱ፤ የምርጫው አሸናፊ ፓርቲ ኢሀአዲግ እንደሚሆን እንደማያጠራጥር ያትታል። ታገስሻው ከዚህም በተጨማሪ ፤ በቴሌቪዥን ሥርጭቱ እና በድረ ገጹ ከሀገር ሸሽቶ ናይሮቢ ውስጥ ጥገኝነት ስለጠየቀው ጋዜጠኛ የትነበርክ እና ደረሰብኝ ስለሚለው በደል ዘግቧል።

« እንደ ብረት የጠጠረ አገዛዝ ባላት ሀገር» በሚለው ርዕሱ ከ457 የምክር ቤት መቀመጫ 456ቱን ኢሀአዲግ ይዞ የመራው ሀገር እንደሆነ በመግለፅ፣ ጋዜጣው ፤ የተቃዋሚዎችን ነፃ አለመሆን እና ብሶት ያትታል። ከዚህም በተጨማሪ ጋዜጣው ፤ ምናልባትም ነፃ ምርጫ ታይቶበታል ያለውን የ97ቱን ምርጫ እና ከዛም በኋላ ስለተነሳው አመፅ እና በወቅቱም ከ200 በላይ ሰዎች ስለመሞታቸው አውስቷል። ከዚህም በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት ፣ አሸባሪ ቡድናትን በመዋጋት የዩናይትድ ስቴትስ ስልታዊ አጋር መሆኑን ጋዜጣው ጠቅሷል ።
©ዶይቸ ቬለ
ወያኔ ኢሕአዴግ በምርጫ ተሸንፎ እያለ አጭበርብሮ በሥልጣን ለመቀጠል በሚያደርገዉ መፍጨርጨር ለሚከተለዉ ማንኛዉም ሕዝባዊ ተቃዉሞ ተጠያቂ ነዉ -

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን
በ 2007 ብሄራዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ ጀምሮ ያለው ሁኔታ ነፃና ፍትሃዊ አለመሆኑን ባወጡት ሪፖርት አረጋግጠዋል::ወያኔ በምርጫው ቅስቀሳ ሂደት ድብደባ፣ አፈና ፣እስራት ፣ግድያ እና እንግልት በግልጽ ፈጽሟል:: (በምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳቀኝ እና በአርሲ ኮፈሌ የተፈጸመው ግድያ ፤ በእነ በቀለ ገርባ ላይ በበደሌ፣ ጅማ እና በነቀምቴ የተፈጸመውን ድብደባ ልብ ይሏል)
ተቃዋሚዎች ወያኔ ኢሕአዴግን በምርጫ ክርክር አዋረዷት:: ህዝቡ ለመድረክ የሰጠው ድጋፍ ስላስደነገጠው ሃይልን በመጠቀም ጫና ቢያደርግም አልተሳካላትም:: ተስፋ ስቆርጡ ለምርጫው ሁለት ቀናት ሲቀሩት ጠ/ሚኒስትሩ ፓርላማው በማይጠራበት ወቅት ስብሰባ በመጥራት ማስፈራሪያ እና ዛቻ በተቃዋሚዎች ላይ ሰንዝረዋል:: ይህም አስቀድሞ የምርጫውን ውጤት ለመቀልበስ በሃይል ምርጫውን ለማጭበርበር ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ እንደነበር የሚያስይ ነበር :: የኢሕዴግ ካድሬዎች የምርጫው ዋዜማ ሌሊት ከአለቆቻቸው የተላለፈውን ትእዛዝ ለመፈጸም አስቀድመው ኮሮጆ በመሙላት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የፌዴራል ፖሊስ: ሚሊሺያዎች: ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እና አድማ በታኝ ፖሊሶችን በማዝመት የምርጫ ቦርድ ተወካዮችን እና የተቃዋሚ (የመድረክ) የምርጫ ታዛቢዎችን መታወቂያቸውን በመቀማት እያስፈራሩ እየደበደቡ በርካቶችን (90%) ሙሉበሙሉ ማለት ይቻላል ከምርጫ ጣቢያ በሀይል አባረዋል።በርካታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የምርጫ ካርድ ተከልክለዋል። የመምረጥ መብታቸዉን ተነፍገዋል።
ስለሆነም: ፀረ ሠላም እና ፀረ ዴሞክራሲ የዘረፋ ቡድን የፈጸመው ምርጫን ማጭበርበር ፣ የህዝብ ድምፅ መዝረፍ፣ ንጹሃን ዜጎችን መግደል እና የማሰር ድርጊት አጥብቀን እያወገዝን የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ይህን መግለጫ አውጥቷል።
1. ኦፌኮ/ መድረክ በኦሮሚያ ክልል ምርጫዉን ሙሉ ለሙሉ አሸንፏል።
2. የተፈፀመው ድርጊት በማንኛውም አለም አቀፍ የምርጫ መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እና ህገ ወጥ መሆኑን እንገልጻለን:: በጽኑ እናወግዛለን::
3. ይህንን የህዝብ ድምፅ ዝርፊያ እና የምርጫ ማጭበርበር ተከትሎ ለሚነሳው የህዝብ ተቃውሞም ሆነ መንግሥት ለወሰደው እና ለሚወስደው እርምጃ ተጠያቂው እራሱ ኢሓዴግ ነው።
4. የህዝቦች ህገመንግስታዊ መብቶች በተጣሰበት፣ በማፈንና በማስፈራራት ምርጫ አስፈፃሚዎች እና የምርጫ ታዛቢዎች ተባረው ምርጫ ተካሂዷል ለማለት አንችልም።
5. ህዝባችን የመረጠው ድርጅት ኦ.ፌ.ኮ /መድረክ/ የሚያደርገውን ቀጣይ የትግል ጥሪ ዝግጁ በመሆን እንዲጠብቁ እናሳስባለን ።
6. የወያኔን አፋኝ ስርአት እድሜ ለማሳጠር በትግል ላይ የምትገኙ ሃይሎች: ወያኔ ይህን ያህል ረጅም ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆይ የቻለው በራሱ ድርጅታዊ ጥንካሬ ሳይሆን የተቃዋሚ ሃይሎች ትግሉን በተቀናጀ ሁኔታ ያለመምራት በመሆኑ በቀጣይ ለሚደረገው ትግል የፖለቲካውን ክፍተት በመዝጋት ትግሉን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ለማሸጋገር በመተባበር እና ልዩነቶችን በማጥበብ እንድንታገል ጥሪ እናቀርባለን።
2. የተፈፀመው ድርጊት በማንኛውም አለም አቀፍ የምርጫ መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እና ህገ ወጥ መሆኑን እንገልጻለን:: በጽኑ እናወግዛለን::
3. ይህንን የህዝብ ድምፅ ዝርፊያ እና የምርጫ ማጭበርበር ተከትሎ ለሚነሳው የህዝብ ተቃውሞም ሆነ መንግሥት ለወሰደው እና ለሚወስደው እርምጃ ተጠያቂው እራሱ ኢሓዴግ ነው።
4. የህዝቦች ህገመንግስታዊ መብቶች በተጣሰበት፣ በማፈንና በማስፈራራት ምርጫ አስፈፃሚዎች እና የምርጫ ታዛቢዎች ተባረው ምርጫ ተካሂዷል ለማለት አንችልም።
5. ህዝባችን የመረጠው ድርጅት ኦ.ፌ.ኮ /መድረክ/ የሚያደርገውን ቀጣይ የትግል ጥሪ ዝግጁ በመሆን እንዲጠብቁ እናሳስባለን ።
6. የወያኔን አፋኝ ስርአት እድሜ ለማሳጠር በትግል ላይ የምትገኙ ሃይሎች: ወያኔ ይህን ያህል ረጅም ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆይ የቻለው በራሱ ድርጅታዊ ጥንካሬ ሳይሆን የተቃዋሚ ሃይሎች ትግሉን በተቀናጀ ሁኔታ ያለመምራት በመሆኑ በቀጣይ ለሚደረገው ትግል የፖለቲካውን ክፍተት በመዝጋት ትግሉን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ለማሸጋገር በመተባበር እና ልዩነቶችን በማጥበብ እንድንታገል ጥሪ እናቀርባለን።
ትግሉ ይቀጥላል !!!!!!!!
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም፣ ዶ/ር ደብረጽዮን ወይስ ዶ/ር ቴዎድሮስ? ቢቢሲ ቀጣዩ የሀገሪቱ መሪ ስለሚሆነው ሰው ከወዲሁ ይተነብያል -

ቢቢሲ ስለከትናንት በስቲያው አምስተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ ከዘገቡት ታላላቅ ሚዲያዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ ቢቢሲ(BBC)
በዚሁ ዘገባው የምርጫው ጊዜያዊ ውጤት በአንድ ሳምንት ውስት የሚታወቅ እንደሆነ ቢገልጽም እንኳን ገዢው ኢህአዴግ ፓርቲ በዘንድሮው ምርጫ ያን ያክል ፉክክር እንደማይገጥመውና ማሸነፉም ከወዲሁ የተተነበየ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡ የተቃዋሚ ፖለቲካ አባላትን፣ መራጮችንና የፖለቲካ ምሁራንን ተዟዙሮ የጠየቀው ይህ ዘገባ የኢህአዴግ ማሸነፍን የሚደግፍ አስተያየቶቻቸውን ያስነብበናል፡፡ ከዚህ ውጪ ኢህአዲግ ካሸነፈ የሀገሪቱ መሪ ማን ይሆናል የሚለውን ለማጠያየቅ የሞክረው ዘገባው የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ተቀዳሚ ተመራጭ ይሆናሉ የሚለው እንዳለ ቢሆንም ሌሎችም እንደ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም እንዲሁም በምክትል ጠቅላይ ሚነስትር ማእረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪውና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በፓርቲው ውስጥ ቀዳሚ ከሆኑ እጩዎችና አቶ ሀይለማሪያምን ተፎካካሪ ይሆናሉ ከሚባሉት ውስጥ ይጠቀሳሉ ሲል ነው ያተተው።
Monday, May 25, 2015
የሻዕቢያ “የተሀድሶ” ስትራተጂ አካሄዱና አንደምታው

Aክሊሉ ወንድAፈረው
ሜይ 22፣ 2015
በAቶ Iሳያስ Aፈወርቂ የሚመራው Aስመራ ላይ የተሰየመው የሻAቢያ መንግሥት ለ 23
ዓመታት የተከተለውን Aካሄድ Eንዳላዋጣው በመገንዘብ ይመስላል በተወሰነ ደረጃ ለየት
ያለ ገጽታን ለማሳየት Eና ራሱን Aለሳልሶና የሰላም Aባወራ ሆኖ ለመቅረብ በመሯሯጥ ላይ
ይገኛል። ይህ ምን መልክ ይዞ ነው የሚራመደው? ለሀገራችን Iትዮጵያስ ምን Eንደምታ
Aለው? የሚለው የዚህ ጽሑፍ ዋና Aላማው ነው።
የAቶ Iሳያስ Aፈወርቂና የሸAቢያ የኩርፊያና የማን Aለብኝ ዓመታት
Aቶ IሳAስ Aፈወርቂ Eና ድርጅታቸው ሸAቢያ Aስመራ ላይ Eንደመንግሥት ከተሰየሙ
በሁዋላ ስለራሳቸው Eጅግ የተጋነነ Eይታ ይዘው ነው ያካባቢውንም ሆነ Aለም Aቀፉን
ህብርተሰብ የተቀላቀሉት። በዚህም መሰረት በየሄዱበት በሽክላ Eቃ የተሞላ መደብር ውስጥ
Eንደገባ Eንሰሳ በግራም በቀኝም ያገኙትን ሁሉ Eያተረማመሱ ቆይተዋል። በዚህም
መሰረት ባጭር ጊዜ ውስጥ፣
• Eንደ Aውሮፓ Aቆጣጠር ከየመን ጋር በ 19961
• ከጅቡቲ ጋር ከ 1994 Eስከ 20082
• ከሱዳን ጋር ደግሞ ከ1994 Eስከ 200 ድረስ ዲፕሎማቲክ ግንኙነትን Eሰከማቋረጥ
የደረሰ ውዝግብ ውስት ገብተው ነበር3
• ከIትዮጵያ ጋር ደግሞ በ1998 ጦርነት ውስጥ ገብቷል።
ይህ ብቻ ሳይሆን Aቶ Iሳያስ Aፈወርቂ Eና ድርጅታቸው ሸAቢያ ከተለያዩ ሀገሮች ጋር
የሚያጋጥማቸውን Aለመግባባት በኩርፊያና ቶሎ ብለው በማካረር ዲፕሎማቲካ ግንኙነትን
Eስከማቋረጥ በሚደርስ Aካሄድ ለመቋጩት ሲሞክሩ ደግሞ ደጋግሞ ታይቷል። ይህ
Aያያዛቸው ባንድ በኩል ለራሳቸው ከሚሰጡት Eጅግ ተፈላጊ ነኝ፣ ታላቅ Aርበኛ ነኝ፣
ታላቅ የፖለቲካ ሊቅ ነኝ ወዘተ ከሚል Eጅግ የተጋነነ ግምት የሚመነጭ ሲሆን በሌላ
በኩል ደግሞ ያስተሳሰብ ደካማነታቸውን Eና ስሜትን የመቆጣጠር ችሎታቸው Eጅግ
ዝቅተኛ Eንደሆነ የሚወስዱትም Eርምጃ ሊያሰከትልባቸው የሚችለውን ጉዳት ማገናዘብ
Aለመቻላቸውን ያመለክታል።
በዚህ ድንገተኛ ኩርፊያ Eና ነገርን ቶሎ የማካረር ባህሪይና Eርምጃ Iሳያስ Aፈወርቂ Eና
ድርጅታቸው ሸAቢያ ራሳቸውን Eጅግ የከፋ ችግር ውስጥ የጣሉበት (ከIትዮጵያ ጋር
ከነበረው የ 998ቱ ጦርነት ውጭ) Aንድ ምሳሌ Eንዳውሮፓውያኑ Aቆጣጠር በ 2007
ከምስራቅ Aፍሪካ በይነ መንግስታት የልማት ድርጅት (Iጋድ) ውስጥ ኤርትራ ራሷን
ድንገት ማግለሏን በጽሁፍ ባስታወቀች ጊዜ ነበር4
።
1 http://www.ipsnews.net/1996/08/yemen-eritrea-hanish-islands-conflict-ends-questionsremain/
2 http://military.wikia.com/wiki/Djiboutian%E2%80%93Eritrean_border_conflict
3 http://news.bbc.co.uk/2/hi/africa/590910.stm
4 http://reliefweb.int/report/eritrea/eritrea-suspends-membership-igad
ይህ Eጅግ ድንገተኛ ያልተለመደና በዲፕሎማቲክ Aለምም Eንደ በሳል Eርምጃ
የማይታየው Aካሄድ Aቶ Iሳያስ Aፈወርቂን ፣ ድርጅታቸውንና Eወካላታለሁ የሚሏት
ኤርትራን ከAካባቢያዊ፣ Aህጉራዊውና Aለም Aቀፋዊ መድረክ Aግልሏቸው በምንም
መልኩ ድምጻቸው Eንዳይሰማ Aድርጓቸው ከEለት ወደ Eለት የተነጠሉ ብቸኛ ሆነው
ቆይተዋል።
ይህ ብቻ Aይደለም፣ Iሳያስ Aፈወርቂ Eንዳውሮፓውያን Aቆጣጠር በ2008 Aመተ ምህረት
ድንገት ተነስቶ Aለም Aቀፍ የEርዳታ ድርጅች ሁሉ ጠቅልላችሁ ከኤርትራ ውጡልኝ
ኣሉ፡፡ በወቅቱ የኤርትራ ህዝብ ችግር Aለበት፣ በረሀብም የሚሰቃየው ህዝብ ቁጥር ሰፊ
ነው፣ ይህን ጉዳይ ለመታደግ Eርዳታው ያግዛል ቢባሉም፣” ነገሩን ሁሉ Aጡዘው
“Eርደታችሁን ረሀብተኛ ለሆኑት ስድስት Eና ሰባት ሚሊዮን Iትዮጳያውያን ሕጻናት
ወይም በቅኝ ግዛት ለተያዙት (Oኪፔሽን ) የOጋዴን ሶማሌ ህዝብ ስጡት ነበር ያሉት” 5
ጉድ ሳይሰማ መስከረም Aይጠባም Eንዲሉ የEርዳታ ድርጅቶችን ድንገት ተነስተው
በጅምላ ማባረራቸው ያሰከተለው ትዝብት ሳይቀዘቅዝ፣ በሜይ 2008 ከAልጀዚራ
ቴሌቪዥን ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ፣ ተመልካችን ሁሉ በሚያሰደነግጥ ሁኔታ
ራሳቸውን ለመቆጣጠር Aቅቷቸው የተሳከረ Eና ካንድ “የሀገር መሪ” የማይጠበቅ
Aቀራረባቸው ሲታይ በሌሎች ዘንድ የነበራቸውን ጥቂት ከበሬታ ያሳጣቸው ይመስለኛል።6
ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ፤ “Aንችው ታመጭው Aንችው ታሮጭው” Eንደሚባለው
በ2007 ድንገት ተነስተው በኩርፊያ ከIጋድ ለቅቄ ወጥቻለሁ Eንዳላሉ ሁሉ በ2011
ደግሞ ድንገት ወደ ድርጅቱ Aባልነት ልመለስ ብለው የIጋድን በር ያንኳኩት ያው Aቶ
Iሳያስ ነበሩ። ይህ ብቻ ሳይሆን ወደ Iጋድ ለመመለስ ያቀረቡት ጥያቄ ደርሶናል ሆኖም
የዚህ Aይነቱ ጉዳይ ውሳኔ የሚሰጠው በድርጅቱ የመሪወች ጉባኤ ስለሆነ በትEግስት
ይጠብቁ ተብሎ ቢነገርም Eንዴት ይሆናል Aሁኑኑ ካላስገባችሁኝ ብለው በዲፕሎማሲው
Aለም Eጅግ ባልተለመደና Aሳፋሪ በሆነ መልክ ሳይጋበዙ መልክተኛ ልከው በስብሰባው
ጉባኤ ላይ ካልተሳተፍኩ ብለው ግርግር የፈጸመት ያው Aቶ Iሳያስ Aፈወርቂ ነበሩ።78
Eነዚህ ከላይ የተጠቀሱት መረጃወች Eንደሚያሳዩት፣ የAቶ Iሳያስ መንግስት ከምስረታው
ጀምሮ Eኔ ያልኩት ካልሆነ በሚል ዘዬ ፣ ባካባቢው የራሳቸውን የበላይነት ለማስፈን
ባደረጉት ሙከራ Eጅግ Aጥፊ የሆነ ባህሪን ሲያንጸባርቁ ለረጅም ጊዜ ቆይተዋል። ይህ
ሁኔታም፤ በስርAቱ ላይ Eጅግ ብዙ ተቃውሞ Aስነስቶባቸዋል፣ ከAካባቢውም ሆነ ከAለም
Aቀፉ ህብረተሰብ ነጥሏቸው ቆይቷል።
Aዲሱ የሸAቢያ Aካሄድ
5 https://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=UAXKsZ8OsWo
(ከ12ተኛው ደቂቃ ጀምሮ ያለውን ያዳምጡ)
6 https://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v=UAXKsZ8OsWo
7 http://www.diretube.com/ethiopian-news/eritrean-representative-thrown-out-of-igad-meeting-inethiopia-video_e219074e8.html
8 http://www.africareview.com/News/IGAD+bars+Eritrea+from+Addis+Ababa+mee
ting/-/979180/1224476/-/5wmtfkz/-/index.html
Aቶ Iሳያሰ ወደስልጣን ሲመጡ ዴሞካራሲያዊ ብቻ ሳይሆን Aብዮታዊም ተብሎ
ሰለተገመቱ Eሳቸውም ቢሆኑ ዴሞካራሲን Eውን ለማድረግ Eችላለሁ በማለት Aለም
Aቀፉን ህብረተሰብ ለተወሰነ ጊዜ ከጎናቸው ለማሰለፍ ችለው ነበር። Aሁን ከ 20 Aመታትን
ያስቆጠረው ተግባራቸው ግን ዴሞክራሲያዊም፣ ዘመናዊም መሪ Eንዳልሆኑ በተግባር ሰላሳየ
ባካባቢው የሚከሰቱ ቀውሶችን EንደEግር ማስገቢያ በመጠቀም ታላላቆቹን መንግስታት
መልሶ ለመወዳጀት ከፍተኛ መገለባበጥ ለማድረግ ሲጣጣሩ ይታያል። ይህን ሲያደርጉ ግን
ቀደም ሲል ይዘዋቸው የሚጓዟቸውን ፍላጎቶች ፣ ለምሳሌ በሀገር ውስጥ ስልጣንን
በብቸኛነት ይዞ መቀጠሉን፣ Iትዮጵያን በተመለከተ ድንበሩን በሚፈልገው መልክ
ማስከለል Eና ከ1998 ጦርነት በሐላ የተቋረጠበትን ጥቅም መልሶ መመስረት በዋናት
ሳይቀየር ነው።
የAቶ Iያሳያስ Aዲሱ Aካሄድ በዋናነት የተጀመረው ባውሮፓውያኑ Aቆጣጠር በ2011
Aምባሳደር ግርማ Aስመሮምን ባፍሪካ Aንድነት ድርጅት Aምባሳደር Aድርገው በሾሙበት
ጊዜ ነበር። የAቶ ግርማ ሹመት ተራ Aምባሳደርነት ሙያ መጫወት ብቻ ሳይሆን የAቶ
Iያሳያስን Aዲሱን ዲፕሎማቲክ Aካሄድ በዋናነት Eንዲመሩም ነበር። Aምባሳደር ግርማ
በሀይለስላሴ ዘመን የIትዮጵያ Eግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ተጫዋች የነበሩና ሁዋላም
በIትዮጵያ ውስጥ የAቶ Iሳያስ መንግስት Aምባሳደር ሆነው ያገለገሉ ናቸው ። በዚህም
የተነሳ የIትዮጵያን ፖለቲከኞችና የዜጎችንም ባህሪይ “ ጠንቅቄ Aውቃቸዋለሁ” ባይ
ናቸው። Aምባሳደር ግርማ በቀጣይነት ይህንኑ የAቶ Iሳያስን Aጀንዳ በዋናነት
ለማስፈጸም በተባበሩት መንግስታት ዋና Aምባሳደር ተደርገው በ2014 መሾማቸው
ይታወሳል።9
ፈረንጆች “ብዙ ትንኞችን ከኮምጣጤ ይልቅ ማርን በመጠቀም ማጥመድ ትችላለህ” “ You
can catch more flies with honey than with vinegar “ Eንደሚሉት የAቶ Iሳያስ
መንግስትም Aላማውን፣ ራEዩን ወዘተ ሳይለውጥ ተቀባይነት ያሰገኛል ብሎ በገመተው
ሰላም Eና መረጋጋትን ባካባቢው ለማሰፈን፤ በግንባር ቀደምነት Aስተግባሪ መስሎ
መሯሯጥን መርጠወል። ለዚህም የሚከተሉትን Eንመልከት
በየመንና መካከለኛው ምስራቅ
ኤርትራን “ከIትዮጵያ ግኝ ገዥነት ነጻ ለማውጣት” Aቶ Iሳያስና ድርጅታቸው ባካሄዱት
ትግል የAረቡ Aለም በሁሉም መልኩ ግንባር ቀደም Aጋር Eንደነበር ይታወሳል።
በገንዘብና በዲፕሎማቲካ ብቻ ሳይሆን ለምሳሌ የIራኑ Aያቶላ ኮሚኒ በሳምንታዊ የEለተ
Aርብ (የጁምA) ሳይቀር ለኤርትራ ነጻነት ተከታታይ ጸሎት ያደርጉ ነበር።10
ከ“ነጻነት” በሁዋላ ግን Eንደተመኙት Eንክብካቤው Aልቀጠለም። በAረቡ Aለምና
በመካከለኛው ምስራቅ ቦታ ተነፍጓቸው የቆየት Aቶ Iሳያስ የየመን ግጭትና የሳውዲ
የሚመራው ትብብር ጣልቃገብነት ሲከሰት በግንባር ቀደምትነት ነው “ሁኔታውን
ለማረጋጋትና ሰላም ለማውረድ” በሚል ሰበብ ዘለው የገቡት። በዚህም መሰረት በAፕሪል
9 http://www.caperi.com/new-permanent-representative-of-eritrea-to-un-presentscredentials/
10 https://www.youtube.com/watch?feature=player_embedded&v (ከሰባተኛው ደቂቃ ጀምረው ያዳምጡ)
2015 በሳውዲ Aረቢያ ጉብኛት Aድርገው በዚሁ ጉዳይ ላይ ከሳውዲ ንጉሰ Eና ሌሎችም
ባለስልጣናት ጋር ተወያይተው Aንዳንድ ስምምነትም ላይ Eንደደረሱ ተዘገቧል።11
በማስከተልም “ባካባቢው ሰላምን ለማምጣት” በሚል ሰበብ ቀደም ሲል ይረዷቸው ነበር
Eየተባለ በሚጠረጠረው የሁቲ Aማጽያን ላይ ጀርባቸውን Aዙረው በሳውዲ ለሚመራው ጸረ
ሁቲ ወታደራዊ ዘመቻ Eግረኛ ጦር ለመላክ Eንደሚፍልጉ ተናግረዋል።12
የAቶ Iሳያስ መንግስት በAንድ Eስላማዊ ሀገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ገብቶ መገኘቱ
በራሱ በኤርትራ የEስልምና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ ሊያስከትለው የሚችለው Eንደምታ
ምን Eንደሚሆን ወደፊት የሚታይ ይሆናል። Aሁን ባለው ሁኔታ ግን፣ በውስጥ የሚመጣን
የህዝብ ቁጣ ለሳውዲ Aረብያና Aጋሮቿ ድጋፍ በመስጠት ሊመጣ ከሚችለው ጠቀሜታ
ጋር ሲወዳደር ሚዛን Aይደፋም ተብሎ Eንደተደመደመና ሊመጣ የሚችለውንም ግፊት
ለመቋቋም ቆርጠው Eንደተነሱ ያመለክታል።
በደቡብ ሱዳን
ቀደም ባሉት Aመታት ኤርትራ የደቡብ ሱዳን ነጻነት ደጋፊ ሆና መኖሯ ይታወቃል።
ደቡብ ሱዳን ነጻነቷን ከተቀናጀች በሁዋላ ግን Aቶ የIሳያስ ተጽEኖ Eዚህ ግባ የሚባል
Aልነበረም፡ በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ድርጅቶች የEርስበርስ ግጭት ሲከሰትም Aቶ Iሳያስ
ችግሩን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ምንም ቦታ Aላገኙም ነበር።
በIጋድ Aጋፋሪነት ተይዞ በነበረው የደቡብ ሱዳን ተፋላሚዎች Eርቅ ጉዳይ
በወያኔ/IህAዴግ ሊቀመንበርነት Eና በሌሎች የምሰራቅ Aፍሪካ መንግስታት ተባባሪነት
Eየተካሄደ ቆይቷል። በዚህ ሂደትም ኤርትራ ሙሉ በሙሉ ተገልላ ቆያታለች። በማርች
2015 የEርቅ ሂደቱ Eንደተደናቀፈ ግልጽ ሲሆን ነበር ኤርትራ ድንገት በዚህ ሁኔታ
ውስጥ ዋና ተዋናይ ሁና ለመቅረብ የሞከረችው። በዚህም መሰረት የደቡብ ሱዳኑን መሪ
Aስመራ ድረስ በመጋበዝ ላካባቢው ችግር ኤርትራ ዋና ተጫዋች ነች የሚለውን ማስጨበጥ
ነበር የሞከሩት። ዋና ምክራቸውም “ሊበጠብጢAችሁ ከሚፈልጉ መንግስታት ተጠንቀቁ”
የሚል ነበር።13
በAለም Aቀፍና ያካባቢ ድርጅቶች ውስጥ (Iጋድ)
ኤርትራ በ2007 ድንገት በቃኝ ብላ ከIጋድ Eንዳልወጣች Eና በወቅቱ ይህ Eርምጃችሁ
ትክክል AይደለምEና Aስቡበት ቢባሉም Aሻፈረኝ ብሎ የቆየው የAቶ Iሳያስ መንግሰት
ማንም ሳይጠይቀው ነበር ድንገት ተነስቶ በ2011 መልሶ ለመቀላቀል ጥያቄ ያቀረው።14
ይህ ጥረት Aቶ Iሳያስ ቀደም ሲል ያጡትን ቦታ መልሶ ለመያዝ የሚደረገው ሙከራ
Aንድ Aካል ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።
11 https://www.middleeastmonitor.com/news/middle-east/18347-saudi-arabia-eritreaagree-to-boost-red-sea-security
http://www.madote.com/2015/04/pictures-eritreanpresident-visits.html
12 http://ethiomedia.com/100leads/4825.html 13 http://sudantribune.com/spip.php?article54751
14 http://stesfamariam.com/2014/04/10/eritreas-igad-suspension-and-reactivation-decisionssacrosanct-and-legal/
ከIትዮጰያ ጋር
Iትዮጰያን በተመለከተ Iሳያስ Aፈወርቂ Aሁን የሚከተሉት Aካሄድ
• መሰረታዊ መስሎ የሚታያቸውን የድንበር ጉዳይ Eሳቸው በሚፈልጉት መንገድ
Eንዲደመደም ማድረግ
• ተቃዋሚውን በማግባባት፣ በመሞት ላይ ካለው የወያኔ ስርAት ጋር ማበር ሳይሆን
የመጭው ጊዜ ባለስላጣናት ጋር መወዳጀት
• ከIትዮጵያዊ ተቃዋሚዎች ጋር በማበር የቆሽሽውን የራሳቸውን ገጽታ ማደስና፣
ተቀባይነት ማግኘት
ጥቂቶቹ ናቸው።
ለIሳት ሰራተኞች በፌብሯሪ 2015 በኤርትራ ውስጥ የሰጡት Eጅግ ረጅም ቃለምልልስ
ተቃዋሚውን ለማግባባት ያዘጋጁት Eቅድ Aንድ ገጽታ ይመስላል። በዚያ ቃለ ምልልስ
ውስጥ Aቶ Iሳያስ፤ የ ኤርትራና Iትዮጵያን ጉዳይ የተመለከተ ስብሰባ በያካባቢው
መደረግ ያገባዋል “ በማለት የሰነዘሩት ምክር መሰል መመሪያ ፤ በቅርቡ ደግሞ በማይ 9
Eና 10 በዋሽንግተን ዲሲ “ ያፍሪካ ቀንድ ሁኔታን” የመረመረው ስብሰባ ይዘት በከፊልም
ቢሆን ከAቶ Iሳያስንና ከሻAቢያን የተሀድሶ ስትራተጂ ጋር Eጅግ Eንደሚጣጣም
ይታያል።
Aቶ Iሳያስ በIሳት ቃለመጠቅ ላይ Aበክረው የገለጹት ለIትዮጵያ Aንድነት የቆሙ፣
ለIትዮጵያ ከመልካም ነገር ውጭ የሚመኙት ነገር Eንደሌለ ፣ የIትዮጵያ ህዝብ መብት
Aለመከበር Eንቅልፍ Eንደነሳቸው Eና Eንዲያውም Iትዮጳያ መፈራረስ Aለበት ተብሎ
በተለያዩ መንግስታት ሲሰነዘር Eርሳቸው Aይሆንም ብለው Eንዳስቆሙ ወዘተ ነበር።
ይሀ ሁሉ ግን Iትዮጰያውያን ለAመታት ከምናውቀው የIሳያስ Aፈወርቂ ንግግሮች Eና
ተግባር ጋር Eጅግ የሚጋጭ ነው።
ሰበብ ፈልገው በIሳያስ Aፈወርቂ ለመጭበርበር በተጠንቀቅ ከሚጠባበቁት ወይም
በIትዮጵያ ኪሳራ ላይ ወዳጅነትን ለመመስረት ከሚፈልጉት በስተቀር ሁኔታውን
በትክክል ለመረዳት ለሚሞክር ሁሉ የAቶ Iሳያስ Aቋም Aሁንም ቀድም ሲል ከነበረበት
ቦታ ፈቀቅ Eንዳላለ መገንዘብ ያቻላል። ለዚህም በዚያው በIሳት ቃለምልልስ Eና
በተለያዩ የዜና Aውታሮች ውስጥ ደግመው ደጋግመው የ ኤርትራና የIትዮጵያ ድንበር
ጉዳይ ያለቀለት Eንደሆነና Iትዮጵያም “ከወረረችው የኤርትራ ግዛት መውጣት Eንዳለባት
መናገራቸውን ማስተዋል በራሱ በቂ መረጃ ነው” ባለፈው Aመት (2014) Aምባሳደር ግርማ
Aሰመሮም ለ ገለልተኛ Aገራት ስብሰባ ካደረጉት ንግግር ውስጥ ደግመው ደጋግመው
ያሰመሩበትም ይህንዩ ነበር። http://www.madote.com/2014/05/ambassador-girmaasmeroms-speech-at.html
በመጨረሻም በቅርብ በሜይ 9 Eና 10 የተካሄደው የዋሸንግተኑ የሰብAዊ መብት ስብሰባ
ጉዳዩ ስለ Aፍሪቃ ቀንድ ነው Eየተባለ፣ በመላው Aፍሪካ በመብት ረገጣ ያፋሪካዋ ሰሜን
ኮርያ (the north Korea of Africa) Eየተባለች የምትታወቀውን ኤርትራ የምታካሂደው
ግፍ በጨረፍታ Eንኳ Aለመናገሩ (Aንዳንድ ጠቃሚ የውይይት ዶክመንቶች መቅረባቸው
Eንዳለ ሆኖ) ጉባIውን ከሰብAዊ መብት ጉባኤነት ይልቅ የሻቢያ የህዝብ ግንኙነት መሳሪያ
Aስመስሎታል። ስለ ኤርትራ መናገር ካላሰፈለገ፣ ስብሰባውን የምስራቅ Aፍሪካ ብሎ
Aለመሰየም ነበር። የምስራቅ Aፍሪካ ከተባለ በሁዋላ ዋናዋን ሰብAዊ መብት ረጋጭ
Aለመተቸት ግን Eጅግ Aሰተዛዛቢ ብቻ ሳይሆን የIትዮጵያውያንን Eና ያርትራ
ወገኖቻችንንም ቁስል Aለመረዳት ነው።
የዚህ Aይነቱ Aያያዝ ደግሞ ለኤርትራም ሆነ ለቀሪው Iትዮጵያ ህዝብ የሚሰጠው
ጠቀሜታ የለውም። የAቶ Iሳያስ ዘግናኛ Aገዛዝ Eንኳንስ የኤርትራ ነዋሪዎች Aለም
Aቀፉ ህብረተሰብም በያደባባዩ የሚናገረው Eና Aበክሮ የሚታገለውም ነው።
ቢያንስ ቢያንስ Eኛ Iትዮጵያውያን Eንደ ዋቢ Eየጠቀስን የምንሟገትባቸው ድርጅቶች
ማለትም ሂውማን ራይትስ ዋች፣ 15 Aምንስቲ Iንተርናሽናል Eና ሌሎቹም ስለ Aቶ
Iሳያስ Aገዛዝ Eና የኤርትራ ነዋሪዎች ሰቆቃ የዘገቡትን በጥቂቱ ማየት በቂ ግንዛቤን
ይሰጣል።
የህዝቡን ትግልም ሆነ ነጻነት ማንም ሀይል Aያግደውም። የሌላው መብት ሲረገጥ የሁሉም
መብት Eንደተረገጠ ማሰታወስ ለሁሉም ተገቢ ነው። ሰለኤርትራ ነዋሪዎች መብት መረገጥ
Eኔ ምን Aገባኝ የሚል ሰው ደግሞ፣ የኔ መብት ስለተረገጠ ለመብቴ በማደርገው ትግል
ሌሎች Eርዳታ ይስጡኝ ብሎ መጠየቁ መሰረት የሌለው ነው16
በመጨረሻም የኤርትራን ጉዳይ በተመለከተ ብዙ Eጅግ ብዙ የሚያነጋግሩ ጉዳዮች Eንዳሉ
መረዳት ተገቢ ነው፡ ይህን ለመረዳት ደግሞ በሀገር ቤት የሚነቃነቁ የIትዮጵያ ተቃዋሚ
ፓርቲወች (Aድርባይ የሚባሉት ሳይቀሩ) የሚሉትን ማዳመጥ በቂ ነው። በዚህ ውስጥ
ያልተዘጋውን የሀገራችንን Aጀንዳ ወደጎን ከማለት Aልፎ ለAቶ Iሳያስና ለመንግስታቸው
ፕሮፓጋንዳ፤ የህዝብ ግንኙነትና Aገዛዙን የማጠናከር ስራ ተባባሪ መሆን ግን ሀላፊነት
የጎደለው ብቻ ሳይሆን መስመር ማለፍም ጭምር ይሆናል።
ማጠቃለያ
የAቶ Iሳያስ ያለፉት ጥቂት Aመታት የተሀድሶ Eንቅስቃሴ Aገዛዛቸውን ከደረሰበት
የውስጥም የውጭም መገለል Eና የፖለቲካ ግፊት፣ Aላቅቆ Eንደገና ለማንሰራራት
የሚደረገው ጥረት Aካል ነው።
Aለም Aቀፍ ሁኔታው ያመቸኛል ባሉት መንገድ Aቶ Iሳያስ ራሳቸውን Eንደገና
Aጠናክረው Eየተንገዳገደ ያለው Aገዛዛቸውን መልሰው ለማጥናከር፣ Iትዮጵያን በተመለከተ
ደግሞ ነባር Aቋማቸውን ለማስፈጸም ያልተዘጉና በEንጥልጥል የሚገኙ Aጀንዳወችንም
በAለም Aቀፍ ግፊትና በተባባሪ Iትዮጵያውያን ለማስፈጸም ሁኔታውን Aያመቻቹ
ይገኛል።
Aንድ የAለም Aቀፍ ሁኔታዎችን የሚተነትን ጸሀፊ የዩክሬን ነጻነት ከየትኛውም ሀያል
መንግስት በላይ በደካማዋና ትንሿ ቡልጋሪያ መዳፍ ስር ሊሆን Eንደሚችል ገልጦ ነበር።
ይህን ያለውም፣ ራሽያ የIኮኖሚዋ መሰረት የሆነው የነዳጅ ምርቷን ወደውጭ ለማስተላለፍ
Eየሰራችው ያለችው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧ በቡልጋርያ በኩል ስለሆነ ደካማዋ
ቡላጋሪያ የቧኒቧውን ስራ Aልደግፍም ብትልና ብታቋርጠው ምን ያህል ታላቋን ራሽያን
ለማሽመድመድ Eንደምትቸል ለማሳየት ነበር።
የEኛም የነጻነት ትግላችንና ሀገራዊ ነጻነታችን በመሞት ላይ ለሚገኝ ጨካኝ ጸረ
Iትዮጵያ ሀይል ማንሰራሪያ ብቻ ሳይሆን በዚሁ ቡድን መዳፍ ስር በድጋሜ Eንዳይወድቅ
15 http://www.hrw.org/world-report/2014/country-chapters/Eritrea
16 https://www.youtube.com/watch?feature=player_detailpage&v=e2rP5alopBE
በጥንቃቄ ማሰተዋል ይገባል። ለዚህም በሬ ሆይ ሳሩን Aይተህ ገደሉን ሳታይ የሚለውን
የAበውን ብሂል Eናሰታውስ። ጎበዝ ነገሩ ሁሉ Eየተስተዋለ ቢሆን መልካም ነው።
4 የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ታዛቢዎች ተደበደቡ * በክፍለሃገራት ኢሕአዴግ ራሱን በራሱ እየመረጠ ነው -

የወያኔው ሚዲያ ኢሕአዴግ አ.አን እና ጎንደርን 100% አሸነፈ ሲል ዘገበ * ዶ/ር መራራና ዶ/ር በየነ ተሸነፉም አለ የወያኔው አይጋ -

Hiber Radio: ዶ/ር አክሎግ ቢራራ እና የአረናው አምዶም ገ/ሥላሴ ልዩ ቃለምልልስ ስለምርጫው * አገዛዙ የሕዝቡን ድምጽ ወደጎን አድርጎ ለራሱ የሰጠውን የምርጫ ውጤት ይፋ ለማድረግ ተዘጋጅቷል * በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎች የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር መጠየቅ ጀምረዋል * በአዲስ አበባ የ17 ዓመቷን ወጣት ሃና ሌላንጎን የደፈሩት ከ17 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸውና ሌሎችም -

< …የምርጫው ውጤት አስቀድሞ የተገመተ ገዢው ፓርቲ የፈለገውን ድምጽ ለራሱ የሚሰጥበት የይስሙላ ነው … በአገር ውስጥም በውጭም ያለው ለውጥ እንዲመጣ የሚሰራው ሀይል ግን በአንድነት ፈጣን ውሳኔ መውሰድ አለበት። በአገር ውስጥ አብዮት መቀስቀስ እንዲችል… >
ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የአገር ቤቱን የይስሙላ ምርጫ አስመልክቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)
<…በምርጫው ድምጽ መሰረቅን አስመልክቶ ገበሬውም ተማሪውም መምህሩም በአጠቃላይ ሁሉም ተመሳሳይ ግንዛቤ አለው። ድምጼ እንዳይሰረቅ ብሎ ነበር በድፍረት ስቃይ እየደረሰበት ታዛቢ ልሁን ለው….ተቃዋሚዎች ተባብረው በጋራ የህዝቡን ድምጽ ለማስከበርና አስገድደው ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለማምጣት መታገል ለባቸው …>
የአረና የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት አምዶም ገ/ስላሴ (ከመቀሌ ምርጫውን አስመልቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ )
በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን አጣብቂኝ እና የተባበሩት ሀይሎች የአየር ድብደባ ያደረሱት ጉዳቶች(ልዩ ዘገባ)
የኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ በቬጋስ(ከበዓሉ አዘጋጆች አንዱ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ)
አስተያየት በአገር ቤቱ ውጤቱ አስቀድሞ የታወቀ ምርጫ ላይ
ሌሎችም
ዜናዎቻችን
የተቃዋሚ የምርጫ ታዛቢዎች ጥቃት ሲፈፀምባቸው ዋለ
አገዛዙ የሕዝቡን ድምጽ ወደጎን አድርጎ ለራሱ የሰጠውን የምርጫ ውጤት ይፋ ለማድረግ ተዘጋጅቷል
ሕዝቡ በተዘረፈው ድምጹ ጉዳይ ተቃውሞ እንዳያቀርብ በሚል የሰብዓዊ ጥሰቱ ቀጥሏል
በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎች የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር መጠየቅ ጀምረዋል
በአዲስ አበባ የ17 ዓመቷን ወጣት ሃና ሌላንጎን የደፈሩት ከ17 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸው
ኬኒያዊው ጠበቃ ፕሬዝዳንት ኦባማ ልጃቸውን ከዳሩልኝ ለጥሎሽ 50 ከብቶች 70 በጎችና 30 ፍየሎች እሰጣለሁ ማለቱ ተሰማ
የኤርትራ መንግስት ለአገሪቱ ወጣቶች ስድትና ሞት የሰብዓዊ ተሟጋች ድርጅቶች ጭምር ይጠየቃሉ አለ
ኢትዮጵያና ኤርትራ በኮንፊዴሬሽን እንዲዋሃዱ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ጠየቁ
የሔጉ ውሳኔ በአዲስ መልክ እንዲቀየር አንድ ታማኝ የተቃዋሚ መሪ ገልፀዋል
ሁቨር በኔቫዳ ስራ እንዲጀምር ህጉ ፀደቀ
ስራ ከመጀመሩ በፊት ለተቆጣጣሪው ኩባንያ ማመልከት አለበት ተብሏል
የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉን
በአዲስ አበባ አቃቂ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የተቃጠለው የአረቄ ፋብሪካ የኩማ ደመቅሳና አዲሱ ለገሰ ንብረት መሆኑ ታወቀ -

ፋብሪካው እየተቃጠለ በነበረበት ወቅት ሲመለከት የነበረው ነዋሪው ማህበረስብ፣ እሳቱን ለማጥፋት ምንም አይነት እገዛ ማድረግ ያለመቻሉን የተመለከቱት የስርዓቱ ካድሬዎች ወሮበላ ተከታዮቻቸውን በማሰባሰብ ነዋሪውን ህዝብ ማን አቃጠለው ከእናንተ አልፎ ሌላ የሚያውቅ የለም ተናገሩ እያሉ ላይና ታች ቢሉም እንኳን ነዋሪው ህዝብ ግን እኛ የምናወቀው የለንም የምታውቁት ካለ ደግሞ እናንተ ንገሩን በማለት ለጥያቄአቸው በጥያቄ መልክ በመመለስ ምንም አይነት መረጃ ከመስጠት እንደተቆጠበ ለማወቅ ተችሏል።
ሰበር ዜና የተሰረቀውን ምርጫ በማውገዝ በኦሮሚያ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ መጀመራቸው ተሰማ -
ቁጣው የተጀመረው የወያኔ ኢቢሲ በብዙ ቢታዎች ኢሕአዴግ ከ90 በመቶ በላይ እየመራ እንደሆነ በመናገሩ ነው።
ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የምርጫውን ዉጤት ወያኔ ነገ እንደማያሳወቅ ነው።
ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የምርጫውን ዉጤት ወያኔ ነገ እንደማያሳወቅ ነው።
ትግስቱ አወሉ, ልደቱ አይሌው እና አያለ ጫሚሶ ምርጫዉ ችግር እንደሌለበት በኢቢሲ (EBC) ተናገሩ -

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰቆጣ አርሶደአሮች በረሃብ ምክንያት ተሰደዱ

ተፈናቃዮቹ ከክልሉ ባለስልጣናትም ይሁን ከፌደራል መንግስቱ ምንም አይነት እርዳታ አለማግኘታቸውን ገልጸዋል።
ብዙዎቹ ተፋናቃዮች ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሲሆኑ፣ በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ስራ ሰርተው ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ እየጠየቁ ነው።
ተፈናቃዮቹ በዝናብ እጥረት ምክንያት ሰብላቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ገልጸዋል።
መንግስት በአካባቢው ስለተከሰተው ድርቅ እስካሁን የሰጠው ምንም አይነት መልስ የለም።
ኢዴፓ የእሁዱን ምርጫ ውጤት ለመቀበል እንደሚቸገር ገለጸ

አጠቃላይ የምርጫው ሂደት አሳፋሪ ነው ያሉት ፕሬዘዳንቱ በርካታ ምርጫ ታዛቢዎቻችን የታዛቢነት ካርዳቸው ተነጥቆ ከምርጫ ጣቢያዎች ተባረዋል ሲሉ ከሰዋል፡፡ “በዚህ ሁኔታ የሚካሄድ የድምጽ ቆጠራ በትክክል ይካሄዳል ብለን አናምንም፡፡ የዚህን ምርጫ ውጤት ለመቀበልም አስቸጋሪ ሆኖ ነው ያገኘነው” ሲሉ ነው ዶክተርጫኔ ለድሬ ቲዩብ አስተያየታቸውን የሰጡት፡፡
ከዚሁ የፖለቲካ ዜና ሳንወጣ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ፓርቲያቸው ለወደፊቱ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በጥምረት ለመስራት አልያም በርካታ ፓርቲዎችን ባስጠለለው መድረክ ስር ራሱን ለማዋቀር እያጤነበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ አቶ ዮናታን ፓርቲው ስለዚህ ሁኔታ ለመነጋገር ራሱን ዝግጁ እንዳደረገ የገለጹ ሲሆን በዚህ በኩል ራሱን ማጠናከር እንደሚፈልግም ጠቁመዋል፡፡
Friday, May 22, 2015
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ


ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም
ዋ ተማሪ መሆን!(ቁጥር ኣንድ)

(በነገራችን ላይ ይህ ወግ፤ ከዘንድሮው ምርጫ ጋር በግርጌም ሆነ በራስጌ ኣይገናኝም ፡፡ ወጉ ስለጠበሳና ስለ ግጥም ነው፡፡በዚህ ታሪካዊ ወቅት ላይ ስለ ጠበሳና ስለግጥም ማውጋትን እንደ ቅብጠት የምትቆጥሩ ኣርበኞች ከዚህ ተመለሱ፡፡)
ወደ ጨዋታው ስንመለስ፤መንግሥቱ ለማ ኮረዳዋ ከንፈር ላይ ከንፈሩን ለማስቀመጥ የሚያስችለውን የረጅምና ያጭር ጊዜ እቅድ ነደፈ፡፡ ሴትን በመማረክ ረገድ፤ በመንግሥቱ ለማ ጊዜ እና በኣባቱ በኣለቃ ለማ ዘመን መካከል ከባድ ልዩነት ኣለ፡፡በኣለቃ ለማ ዘመን ኣንዲት ሴት ከፈለግካት ጉልበትክን ተጠቅመህ ትማርካታለህ፡፡ መፍትሄው ኣበባ ሳይሆን የወይራ ሽመል ማበርከት ነበር፡፡ በፈረስህ ኣባረህ እንሥራዋን ጀርባዋ ላይ ሰብረህ ወደ ጫጉላ ይዘሃት ትዘምታለህ፡፡
መንግሥቱ ለማ ላቅመ- ኣምሮት በደረሰበት ዘመን ላይ የነበረው ስልጣኔ ሴቶችን ከተጠቂነት ወደ ኣጥቂነት ኣሸጋግሯቸዋል፡፡ ቆነጃጅትን “የሚታዩ እንጂ የማይበሉ ፍሬዎች” ኣድርጓቸዋል ፡፡ በዚያ ዘመን ህጉን ሳትጋፋ ልጂቷንም ሳታስከፋ ኣንዲት ቆንጆ ሴት ከንፈር ላይ ለመድረስ ረጅምና መራራ ትግል ማለፍ ይጠበቅሃል፡፡
“የደጋ ማርና፤ የቆንጆ ልጅ ከንፈር
ወድቀው ካልተነሡ፤ በዋዛ ኣይደፈር”
እንዲል ገጣሚው ሙሉጌታ ተስፋየ፤ በኣበበ ተካ ዜማ፡፡
“የደጋ ማርና፤ የቆንጆ ልጅ ከንፈር
ወድቀው ካልተነሡ፤ በዋዛ ኣይደፈር”
እንዲል ገጣሚው ሙሉጌታ ተስፋየ፤ በኣበበ ተካ ዜማ፡፡
ከእለታት ኣንድ ቀን መንግሥቱ ለማ የከጀላትን ልጅ እንደምንም ኣግባብቶ ሲኒማ ጋበዛት፡፡ሲኒማው እንዳከተመ፤ ቤቷ ድረስ ሸኝቷት በር ላይ ካደረሳት በኋላ በሲኒማው ውስጥ ያሉት ፈረንጆች እንደሚያደርጉት በ“ጉድ ባይ ኪስ” ሊያቀልጣት ከንፈሩን ከሰገባው መዘዝ ኣደረገ፡፡ከዚያ በኋላ ባካባቢው የተሰማው እምጵዋዋዋዋዋ የሚል ሳይሆን ጦዋዋዋዋዋዋ የሚል ድምጽ ነው፡፡የዚያን ቀን ምሽት በመንጌ ፊት ላይ ያረፈው ጥፊ ለኣማርኛ ስነግጥም ትልቅ ኣስተዋጽኦ ኣድርጓል፡፡
በጠራ ጨረቃ
በጠራ ጨረቃ፤ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ፤ እንደ ከዋክብት
ሳማት ሳማት ኣሉት፤ እቀፍ እቀፋት
ኣላወላወለም፤ ወጣቱ ታዘዘ
ወገቧን ኣንገቷን ፤በእጅና እጁ ያዘ
ምንም እንኳ ጡቷ፤ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ፤ የጉማሬ ኣለንጋ
ጆሮ ግንዱን ሰማው ፤በጥፊ ሲናጋ
በጠራ ጨረቃ፤ በእኩለሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን፤ ዋ ተማሪነት
(መንግስቱ ለማ)
በጠራ ጨረቃ፤ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ፤ እንደ ከዋክብት
ሳማት ሳማት ኣሉት፤ እቀፍ እቀፋት
ኣላወላወለም፤ ወጣቱ ታዘዘ
ወገቧን ኣንገቷን ፤በእጅና እጁ ያዘ
ምንም እንኳ ጡቷ፤ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ፤ የጉማሬ ኣለንጋ
ጆሮ ግንዱን ሰማው ፤በጥፊ ሲናጋ
በጠራ ጨረቃ፤ በእኩለሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን፤ ዋ ተማሪነት
(መንግስቱ ለማ)
- በምትመለከቱት ፎቶ ውስጥ የግጥሙ ቀስቃሽ የሆነችው ሜሪ ታደሰ ትታያለች፡፡ ፎቶ ግራፉን ባየሁ ቁጥር ኣይኔ ኣስቀድሞ የሚያርፈው መዳፏ ላይ ነው፡፡“ጆሮ ግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ”የሚለው መስመር ግነት ኣለመሆኑን ለመረዳት የእጇን መዳፍ ግዙፍነት ማየት ይበቃል፡፡
በጎንደር፤ በደብረብርሃን፤ በደሴ የወያኔ የምረጡኝ ፖስተሮች እየተቀደዱ ሲሆን ጎንደር ከዚሁ ጋር ተያይዞ ዜጎች እየታሰሩ ነው -

በጎንደር ከተማ ቀበሌ 04 በኢህአዴግ የተለጠፈውን የምርጡኝ መቀስቀሻ ፖስተር በማየት ለውጥ ለማያመጣ ስርዓት አንመርጥም በማለት እየቀደዱት መሆናቸውን የገለፀው ይህ መረጃ በህብረተሰቡ ተግባር የተናደዱት የስርዓቱ ካድሬዎች ምንም አይነት ወንጀል ላልፈፀመ ዜጋ አንተነህ የለጠፍነውን ፖስተር የቀደድከው እያሉ በማሰር ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ታውቋል፣
የደረሰን መረጃ ጨምሮ- የኢህአዴግን ፖስተር ቀድዳችኋል ተብለው በስርዓቱ ታጣቂዎች ከታሰሩት ውስጥም። ታደሰ ታፈሰ፤ አቶ ጫቅሌና ሌሎችም በርካታ ዜጎቻችን የሚገኙባቸው በእስር ቤት እየተሰቃዩ እንደሚገኙና ህብረተሰቡ ደግሞ በላዩ ላይ እያወረደ ያለውን ግፍ ለማስቆም ለሚመለከታቸው አካላት እያደረገ ያለው አቤቱታ ምንም አይነት ውጤት እንዳላመጣለት ከምንጮቻችን ያገኘውነው መረጃ አመለከተ፣
በተመሳሳይ በደብረብርሃንና ደሴ ከተሞች በየቀበሌው የተለጠፈ የብአዴን/ኢህአዴግን የምረጡኝ መቀስቀሻ ፖስተር ቀለም በመቀባትና በማበላሸት ልማት ይሁን እድገት ለማያመጣ ስርዓት አንመርጥም በማለት ተቃውሞአቸውን በመግለፅ ላይ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ከቦታው አክለው አስታውቀዋል፣
Subscribe to:
Posts (Atom)