Thursday, May 28, 2015

መድረክ ባለፈው እሁድ የተካሄደውን አምስተኛው አገር አቀፍ አጠቃላይ ምርጫ ውጤትን እንደማይቀበል ገለፀ -

11050696_1596569733947557_2286534849872328917_nየመድረኩ አመራር የሆኑትን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ Bbnradio Mereja Mekebeya አግኝቶ ያነጋገራቸው ሲሆን ከርሳቸው ጋር ያደረገነውን ቆይታ በዛሬው ዝግጅታችን ይጠበቁን :: የመድረክ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ በምርጫው ሂደት ላይ ችግሮች የነበሩ በመሆኑ ውጤቱን አንቀበልም ብለዋል። አፍንጮ በር አከባቢ በሚገኘው የመድረክ ዋና ፅህፈት ቤት መግለጫ የሰጡት የመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ሌሎች የመድረኩ አመራሮች ናቸው።
ምርጫ ቦርድ በዛሬው እለት ያወጣው ጊዜያዊ ውጤት ተቀባይነት የለውም ሲሉ የመድረክ ፓርቲ አመራር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለቢቢኤን ገለጹ
ቢቢኤን ዜና
ምርጫ ቦርዱ በዛሬው እለት ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት መግለጫ ኢህአዴግ 100 ፐርሰንት በደረሱ ጊዜያዊ ውጤቶች ማሸነፉን ገልጽዋል፡፡ ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ያለው መድረክ በበኩሉ በዛሬው እለት በሰጠው አስቸኳይ መግለጫ ይህንን እንደማይቀበለውና በምርጫው ጊዜ የደረሱትን ችግሮች በመዘርዘር ለሁለት ሰአታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የመድረኩ አመራር የሆኑትን ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ቢቢኤን አግኝቶ ያነጋገራቸው ሲሆን ከርሳቸው ጋር ያደረገነውን ቆይታ በዛሬው ዝግጅታችን ይጠበቁ
-

No comments:

Post a Comment