
ለፍትሃዊ እና ነጻ ምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ነጻ እና ለቅስቀሳ የሚሆን የመረጃ ማሰራጫ ሚዲያ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብቶች ሲቭክ ማህበራት እንዲሁም የተላያዩ አለም አቀፍ እና ሃገር አቀፍ ሕብረተሰቦች በታዛቢነት ባልተወከሉበት ምርጫ ማካሄድ አያስኬድም ሲል መግለጫው አሽሟጧል::ጋዜጠኞችን በማሰር እና በማሳደድ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገደብ በመስጠት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ጣልቃ በመግባት የፖለቲካ ምህዳሮችን በማጥበብ ምርጫ ማካሄድ አይሞከርም ሲል መግለጫው ተናግሯል::
የአሜሪካ መንግስት ከኢትዮጵያ እና ከሕዝቧጋር ጠንካራ ግንኙነት አለው ያለው መግለጫው ዲሞክራቲክ ተቋማት ዕንዲጠናከሩ የፕሬስ ነጻነተ እንዲያብብ በሃገሪቱ የታፈነው የፖለቲካ ምህዳር ሁሉ ክፍት እንዲሆኑ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአለም አቀፍ ሰባዊ መብቶች ድንጋጌ ግዴታዎች እንድታከብር አብረን እንሰራለን ብሏል::
No comments:
Post a Comment