
የ16 አመቷ ኤልሳ በገፅታዋ ብሶትና መከፋት በሚታይበት መልኩ « አባቴ በተለይም አጐቴ በጣም ይረብሹኛል። “አንቺ ኦሮሞ ነሽ” ይሉኛል። አጐቴ ካርታ እያሳየኝ ኢትዮጵያዊነቴን እንድክድ ይወተውተኛል። በጣም ስለመረረኝ ዳግም እንዲህ እንዲህ አይነት ነገር እንዳያነሱብኝ ነገርኳቸው። ኢትዮጵያዊ ነኝ! አለቀ ደቀቀ! ኢትዮጵያ እያለሁ ያልነገራችሁኝን ለምን እዚህ እየነገራችሁ አገሬን ኢትዮጵያ እንድክድ እንደምትወተውቱኝ አላውቅም፤ አልኳቸው» ካለች በኋላ በሃዘን ስሜት ተውጣ « እናትና አባቴ ተለያይተዋል። አጐቴና አባቴ ፍላጐታቸው እኔ ኢትዮጵያዊነቴን እንድክድ ብሎም በፊት የማላውቀውንና አሁን የገባኝን የእናቴ አማራ መሆን እንዳልቀብል ወይም እንድቆራረጥ ነው እቅዳቸው።
እናቴና ኢትዮጵያ ለእኔ አንድ ናቸው! ሁለቱንም አልክድም! ከዚህ በኋላ ቢያስጨንቁኝ እከሳቸዋለሁ። አዎ እከሳቸዋለሁ! አይረብሹኝ» አለች በቁጣ። በውስጤ ክፉኛ አዘንኩ። በታዳጊዋ አቋም ስለተደነቅኩ ግንባሯን ሳም አደረኩና « ወደ ክስ አትሂጂ።
አሁን በያዝሽው የፍቅር ፅናት አቋም እያስተማርሽ – አሸንፊያቸው!» አልኳት። “እሺ” አለች በሙሉ ፈገግታ።.. አባቶቻችን ያላስተማሩንን ለልጆቻችን የምንሰብከው የጥላቻ መርዝ ፋይዳው ምንድነው?…በየአቅጣጫው የጥላቻና ዘረኛ መርዝ የሚያሰራጩ ወገኖች ከዚህ ድርጊታቸው ቢቆጠቡ ይበጃል! ምናልባት “ወያኔ ያመጣው ነው” ሊባል ይችላል። ነገር ግን ለልጅህ ያንን መንገድ ማሳየት አለበህ?..አንተ ለምታራግበው ጥላቻ ተጠያቂው አንተ ነህ!!…በነገራችን ላይ በተመስገን መላኩና ሰብለ እንዲሁም ሌሎች የተዘጋጀው ድራማ ድንቅ ነበር! “24 አመት የታመመችው ኢትዮጵያ” ነው ያላችሁት በድራማው!?
No comments:
Post a Comment