Sunday, April 26, 2015

በጣም አስደንጋጭ ዜና .. ይህንን አስቸኳይ መልዕክት ሼር በማድረግ በየመን ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንዲደርስ እናድርግ!! በጣም አስደንጋጭ ዜና .. ይህንን አስቸኳይ መልዕክት ሼር በማድረግ በየመን ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንዲደርስ እናድርግ!!

በጣም አስደንጋጭ ዜና .. ይህንን አስቸኳይ መልዕክት ሼር በማድረግ በየመን ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንዲደርስ እናድርግ!!በጣም አስደንጋጭ ዜና ነው። ነገሩ እውነት ከሆነ በጣም ያስፈራል። ከሰሞኑ ሲያስጨንቀኝና አእምሮየን ረፍት ሲነሳው የነበረ ስጋት። የ ISIS ወደ የመን መግባት። በጦርነት የፈራረሱ አገራትን እንደ ምሽግ ተጠቅሞ ሰይጣናዊ የሽብር እንቅስቃሴውን እየፈጸመ የሚገኘው የ ISIS ቡድን ዛሬ የመን ሰንአ መግባቱን አወጇል። አውሬዎቹ ISIS ሶች ዛሬ በለቀቁት የ 9 ደቂቃ ቪዲዮ የሁቲ አማጽያንን አንገት ልንቆርጥ የመን ገብተናል ሲሉ ዝተዋል። ዝርዝሩን ከታች ያስቀመጥኩት ሊንክ በመጠቀም አንብቡት።
ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ በየመን የሚኖሩ አያሌ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ከመቼውም ጊዜ በላይ ጥንቃቄ መውሰድ መጀመር ይኖርባቸዋል። እግዚኦ! ከስቃይ ላይ ሌላ ስቃይ ፈታኝና አስፈሪ ጊዜ እየመጣብን ነው። በየመን ደራሽ ላጡት ወገኖቻችን ደህንነት ተግተን መጸለያችንን አናቋርጥ!! በየመን የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ነቅታችሁ ራሳቸውን ጠብቁ አደራ። ቢቻል በሕብረት እና በአንድነት የምትኖሩበትንና የምትንቀሳቀሱበትን መንገድ አመቻቹ። በተለይ ደግሞ ለአደጋ ሊያጋልጡ ወደ ሚችሉ አስፈሪ ቦታዎች እንዲሁም ወደ ገጠራማ አካባቢዎች ከመንቀሳቀስ ታቀቡ። እናንተም ለጥንቃቄ ይጠቅማቸዋል የምትሉትን መልዕክት ሼር በምታደርጉበት ጊዜ አስቀምጡላቸው።

No comments:

Post a Comment