Thursday, March 19, 2015

የአንድነት ፓርቲ ሰልፎች ቀጥታ ዘገባ ይከታተሉ

udj_25_1የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ፣ በጂንካ፣ በደብረ ማርቆስ፣ በሸዋ ሮቢትና በአርማ ምንጭ ዞን ከንባ ወረዳ፣ አምስት ቦታዎች ሰላማዊ ሰልፎች ይደረጋሉ። የሰልፉ አለማ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ምርጫ ቦርድን እና የሚቆጣጠራቸውን ሜዲያዎች ተጠቅሞ በአንድነት ፓርቲ ላይ የሚያደርገውን ኢ-ሕገ መንግስታዊ ድርጊት ለመቃወም ፣ የሰላም የዲሞክራሲና የነጻነት ለማሰማት፣ ለታሰሩ የሕሊና እስረኞች አጋርነትን ለማሳየት ተብሎ የተጠራ ሰላማዊ ሰልፍ ነው።
11፡ 30 AM አዲስ አበባ ሰዓት
በሸዋ ሮቢት  በሺሆች የሚቆጠሩ ሰልፉን ተቀላቅለዋል። ሰልፉ በጣም ደምቋል። የስርዓቱ ደህንነቶች ህዝቡ እንዳይወጣ ቢያከላክሉም ህዝቡ ግን ጥሶ ወደ ሰልፉ እየመጣ ነው። ህዝቡ በከፍተኛ መነቃቃት ድምጹ እያሰማ ነው። በደብረ ማርቆስም ብዙ ህዝብ በተገኘበት ሰልፉ እየተካሄደ ነው።
በአዲስ አበባ ፣ በዛሬው ዕለት በህወሃት/ኢህአዴግ ፖሊሶች አንድነት ፓርቲ የጠራውን ሰልፍ ለመበተን ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመ፡፡ ድብደባው የአካል ማጉደልንም ያካተተ ነው፡፡ ጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስና አቶ ዳግማዊ ተሰማ ራሳቸውን ስተዋል፡፡ ዳግማዊ አይኑ ማየት አልቻለም፡፡ በአንባገነኑ ስርዓት ከፍተኛ ድብደባ ከተፈፀመባቸው አመራር አባላትና አባላት መካከል፡-
1. አቶ አስራት አብርሃም (የህዝብ ግንኙነት ተጠባባቂ ሃላፊ)
2. አቶ ዳንኤል ተፈራ (የውጭ ጉዳይ ሃላፊ)
3. አቶ ብሩ ብርመጅ (የፖለቲካ ጉዳይ ሃላፊ)
4. አቶ ፀጋየ አላምረው (ምክትል አፈ-ጉባኤ)
5. አቶ አሻግሬ መሸሻ (የሰሜን ቀጠና ሃላፊ)
6. አቶ ሰለሞን ስዩም (የኤዲቶሪያል ቦርድ ሰብሳቢ)
7. ወ/ት ልዕልና ጉግሳ (የም/ቤት አባል)
8. አቶ ዳግማዊ ተሰማ (የም/ቤት አባል)
9. ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጎስ
10. አቶ ስንታየሁ ቸኮል (የአዲስ አበባ የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ)
11. አቶ አሸናፊ አሳምረው (የወረዳ አመራር)
12. አቶ ኢሳያስ ቱሉ (አባል)
13. ወ/ት መስከረም ያረጋል (አባል)
14. አቶ ሃይሉ ግዛው (የወረዳ ሰብሳቢ)
15. አቶ አዲሱ መኮንን (የወረዳ ሰብሳቢ)
16. አቶ ሲሳይ ካሴ (አባል)
17. አቶ ወጋየሁ አድማሴ (አባል)
18. አቶ ክብረት ሃይሉ (የም/ቤት አባል)
19. አቶ ስለሺ ደቻሳ (አባል)
20. አቶ ማሩ አካሉ (አባል)
21. አቶ ክፍሉ በዳኔ (አባል)
22. አቶ ፋሲካ አዱኛ (የወረዳ አመራር)
23. ወ/ሮ ገነት ግርማ (የወረዳ አመራር)
24. ተስፋየ ብዙነህ (አባል) ሲሆኑ በርካቶች የደረሱበት አልታወቀም፡፡ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ህክምና እየተከታተሉ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ሪፖርት እየተከታተልን እናቀርባለን፡፡
የነፃነት ጥያቄው በድብደባ አይቀለበስም!!!
11፡ 10 AM አዲስ አበባ ሰዓት
ለአረጋዉያን የማይራራ አገዛዝ !
10942436_766157653469171_1638673881177919192_n1508091_1540868542851010_2275096741139581552_n10940556_1540868716184326_6973573643655824499_n
11፡00  AM አዲስ አበባ ሰዓት
ከ25 በላይ የአንድነት አባላት ከፍተኛ ደብደባ ደርሶባቸዋል። ስለሺ ሀጎስ ና አስራት አብርሃ በጣም ክፉኛ ተጎድተዋል።፡መሬት ላይ ሁሉ ወድቀው ነበር ዱላ ሲያሳርፉባቸው የነበሩት። ሴቶች  ድብደባ ደርሶባቸዋል። ሆዳቸው ላይ ሁሉ በዱሉ ሲመቱ ነበር።
934894_766156370135966_7920943020857307168_n984265_766156376802632_4998470168309302853_n10408157_766156373469299_2425276408432551502_n10334280_1043007619047538_4471972846935370888_n
10፡30  AM አዲስ አበባ ሰዓት
በገሞጎፋ ዞን ከንባ ወረዳ ሰልፍ ሊጀመር ነው። የወረዳው ከሰማኒያ በላይ የሚሆኑ አደራጆች በፓርቲው ጽ/ቤት ተሰባስበዋል። በወረዳው 30 ቀበሌዎች አሉ። በዚያ የሚኖሩ በእርሻ ሥራ የሚተዳደር ገበሬዎች ወደ አንድነት ጽ/ቤት እየመጡ ነው።
ደብረ ማርቆስ ሰልፉ በአራት ሰዓት ( 10 ኤም)  ተጀምሯል። ብዙ ህዝቡ በሰልፉ ተገኝቷል። የተለያዩ መፈክሮች እየተሰሙ ነው። ድል የሕዝብ ነው !  አንድነት አንድ ነው !  ዉሸት ሰለቸን ፣ ኢሕአዴግ በቃህ፣ ጭኮኖ በቃን፣ ግፍ በጋን፣ ኢሕአዴግ ይወድቃል ! ኢትዮጵያ ነጻነቷን ትሻለች !  ኢቲቪ፣ ኢቢሲ ዉሸት ነህ !     ….የሚሉ መፈክሮች ሰልፈኞቹ እያሰሙ ነው።  በአዲስ አበባ እየደረሰ ያለውን ግፍ እናወግዛለን ሲሉም በአዲስ አበባ የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብዓዊ ግፍ አዉግዘዋል !!!
10፡00  AM አዲስ አበባ ሰዓት
ሰላማዊ ዜጎች በአገራቸውና በምድራቸው እንደ ከብት እየተደበደቡ ነው። እጅግ በጣም ከፍተኛ ጉዳይ ደርሷል።በአመራር አባላቱም ላይ ጉዳት ደርሷል። ህዝቡ አስፋልት ላይ እየጠበቀ ቢሆን፣ ሰልፈኞቹ  ሰልፉን እንዳይመሩ ከጅምሩ በፌዴራል እየተደበደቡ ነው። በሚሊዮኖ ድምጽ ላይ አምደኛ የሆነችው መስከረም ያረጋል ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ዋና አዘጋጅ ስለዚ ሐጎስ፣ በጣም በጭካኔ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል።
የአንድነት የሥራ አስፈጻሚ አባልና የዉጭ ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ የምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ አቶ ጸጋዬ አላምረው፣ የሥራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ አቶ እንግዳ ወልደጻድቅ፣ የምክር ቤት አባል ወ/ር ልእልና እንዲሁም ብዙ የአመራር አባላት ተደብደበዋል። ከፍተኛ ጉዳት ስለደረሰባቸው ወደ ሀኪም ቤት እየተወሰዱ ነው።
አንድነት6ስለሺ2ሲሊሺ1
9፡30  AM አዲስ አበባ ሰዓት
እጅግ በጣም በርካታ ፌዴራል ፖሊሶች በአንድነት ጽ/ቤት አካባቢ ሰፍረዋል። እጅግ በጣም ከባድ ጉዳት በሰልፈኞች ላይ እየደረሰ ነው። በሰደፍ አንድነቶች እየተደበደቡ ነው። የሚሊዮኖች ድምጽ ዋና አዘጋጅ አቶ ስለሺ ሃጎስ እጅግ በጣም ተጎዷቷል። ሴቶች እህቶቻችን እይተደበደቡም ብትፈልጉም ግደሉን እያሉ ወደ ፊት ለመሄድ እየተሞከረ ነው። እጅግ በጣም ጭካኔ የተሞላበት ፣ አረመኔያዊ ተግባር በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየተፈጸመ ነው።ፖሊስ
9፡ 15 AM አዲስ አበባ ሰዓት
ሰልፉ ገና አልተጀመረም። የአንድነት አባላት በጽ/ቤቱ ጊቢ ዉስጥ ደመቅ ያለ ነገር እየፈጠሩ ነው። ፊሽካዉና መፈክሩ እየደመቀ ነው የሚገኘው።
andinet10andinet11andinet12
8፡ 30 AM አዲስ አበባ ሰዓት
የአንድነት ሰዎች እየተሰባሰቡ ነው። በአንድነት ጽ/ቤት
አንድነት5አንድነት3
8፡ 00 AM አዲስ አበባ ሰዓት
ትላንት ቅዳሜ አዲስ አበባን ጨመሮ በበርካታ ከተሞች ቅስቀሳዎች ተደርገዋል። የሰልፉ ቀንም እንሆ አሁን ደርሷል። “በጣም አስገራሚ ነው ! ሰልፉ ላይ ለመታደም ገስግሰው በሌሊት በአንድነት ጽ/ቤት በርካታ ሰዎች እየተገኙ ነው። በሉ እናንተም ፈጠን ፈጠን” – ስለሺ ሃጎስ

No comments:

Post a Comment