
ይሄንን አስመልክቶ በዛሬው ቀን 10/07/07/ ከ 8/ሰሀት በኃላ ያሉበትን ሁኔታ ለማረጋገጥ ወደ ቦታው በመሄድ ጥየቃ ለማድረግ ብንሞክርም ጥየቃ እንደማይቻል ነገር ግን ስንቅ ብቻ ማስገባት እንደሚቻል ተገልጾልን የቅርብ ቤተሰብ የሆነ ሰው ብቻ ከሆናችሁ ግን ወደ ቢሮ ቁጥር/35/ በመሄድ አስመዝግባችሁ መገናኘት ይቻላል ቢባልም ወደ ቦታው በመሄድ ስንጠይቅ እንደዚ የሚባል እስረኛ የለም ተብሉዋል፡፡
ቀደም ሲል እስረኞቹ መኖራቸው ከመዝገብ ተረጋግጦ መጠየቅ የሚችለው ቤተሰብ ብቻ ነው፡፡ በተባልነው መሰረት የጠየቅን መሆኑን ብንገልጽም የተባሉትን ሰዎች አናውቃቸውም በማለት ሁለት የተለያየ ምክንያቶች ሲሰጡ ለማየት ተችሉዋል፡፡
ነገር ግን ወጣት ብርሀኑ ተ/ ያሬድ ከወላጅ እናት ጋር ለጥቂት ደቂቃ ቢሆንም ያገኙት ሲሆን በመልካም ሁኔታ እንደሚገኝ ለቤተሰቡ መግለጹን ለማወቅ ተችሉዋል፡፡ የወያኔ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲን ካፈረሰ በኃላ ድርጊቱን የተቃወሙ አባሎች ላይ ከፍተኛ መንገላታት እና አፈና እየተፈጸመባቸው የሚገኝ ሲሆን ይሄንን አስመልክቶ ከሀያ ቀን በፊት ከሸዋ ሮቤት የታፈነው ወጣት ዘሪሁን ገሰሰ እስካሁን የት እንዳለ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ በማህከላዊ ማጎሪያ እስር ቤት ከሚገኙት ሰላማዊ ታጋዮች ጋርም እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል።
No comments:
Post a Comment