
የአገዛዝ እድሜውን ለማስረዘም የማይቧጥጠው ነገር ያሌለው ሕወሓት በኢሕኣዴግ ድርጅቶች መካከል የተስፋፋው የውስጥ ሰላም ማጣት እና አለመተማመን ስላሰጋው በመጀመሪያ በብኣዴን ውስጥ ያሉትን እና ያሰጋሉ የተባሉ ባለልጣናትን እና ካድሬዎች ማስወገድ ስለሆነ ይህንኑ ስራውን በወያኔ ሚዲያ ላይ ባሰማራቸው ሰዎች ላይ እንደሚጀምር ታውቋል::በተለያየ የስልጣን እርከን ላይ የነበሩ የብኣዴን ሰዎች በእረፍት ስም እቤታቸው እንዲቆዩ የተደረጉ ሲሆን ካድሬዎችም እንዲሁ እረፍት እንዲወስዱ ፎርም እንዲሞሉ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል::ከእረፍት ከመመለሳቸው በፊት ለእያንዳንዱ በግል አርፎ እንዲቀመጥ ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ የደህነንት አካል መዘጋጀቱን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል::
No comments:
Post a Comment