በተለይ አባይ ማዶ በሚባለው አካባቢ ህዝቡ ወደ ባህርዳር ለመግባት ሲሞክር ከትግራይ ነጻ አውጪ ሰራዊት ጋር እንደታኮሰና ቁጥራቸው በይፋ ያልታወቀ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል::
የሕወሓት ነፃ አውጪ ግምባር በተለይ በዛሬው ዕለት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ከስልጣናቸው ካገደና ከማንኛውም የድርጅት ሥራ ውጭ ካደረገ በኋላ የሕዝቡ መነሳሳት እንደጨመረ ከስፍራው የሚደርሱን መረጃዎች ያመለከታሉ:: በተለይም የክልሉ ፖሊስም ከሕዝብ ጋር በመቆም ከትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች ላይ ጥቃት እንደፈጸመም አንዳንድ መረጃዎች ተሰምተዋል::
በባህርዳር ምንም ዓይነት የንግድ ልውውጥ እንደሌለና በከተማዋ ያሉ ባጃጆችም ከአንዳንዶቹ በስትቀር በከተማዋ እንደማይታዩ ለዘ-ሀበሻ የመጣው ዜና ጠቁሟል::
No comments:
Post a Comment