
ዛሬ በደብረብርሃን ከተማ ምንም ዓይነት የባጃጅ ትራንስፖርት አልነበረም ያሉት እነዚሁ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በወልቃይት ጉዳይ ጥያቄ እንዳታነሱ; በጎንደርና በባህር ዳር የተደረገውን የህዝብ ተቃውሞም እንዳትደግፉ; ያንን የሚደግፉ ጸረ ልማቶች ናቸው የሚሉ ማስፈራሪያዎች ከመድረኩ ተሰምቷል::
የባጃጅ ሹፌሮቹ በጎንደርና ባህርዳር ሕዝብ ያነሳውን ጥያቄ አውግዙ ሲባሉ እምቢ ቢሉም የሕወሃት መንግስት ግን “በደብረብርሃን ያሉ የባጃጅ ሹፌሮች በጎንደና ባህርዳር የተደረገውን የሕዝብ ተቃውሞ አወገዙ” የሚል ዜና ከመስራት እንደማይቆጠብ ታዛቢዎች ይናገራሉ::
በደብረብርሃን ወጣቶችን ሳይቀር ቤት ለቤት እሁድ ሰልፍ እንዳትወጡ እያሉ እያስፈራሩ ነው ያሉት ዘጋቢዎቻችን አብዛኛው ሕዝብ ግን እሁድ ሰልፍ ከመውጣት የሚያግደን ምንም የለም የሚል አቋም እንደያዘ ለመረዳት ተችሏል::
No comments:
Post a Comment