
አቶ አማረ በሚያዚያ 14 2007 በአዲስ አበባ ከተማ በተነሳውና ታሪካዊ ከፍተኛ ተቃውሞ ላይ፣ ወጣቶችን በማደራጀት በጥብጠሃል በሚል በቦሌ ክፍለ ከተማ አምቼ እሥር ቤት ይታሰራሉ። ከብዙ መንገላታት በኋላ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ። ወጣቶችን አደራጅተው በጥብጠዋል በተባለበት ቀን፣ ከምርጫ ቦርድ ጋር በሚደረግ ክርክር፣ ሌላ ፍርድ ቤት እንደነበሩ መረጃ ያቀርባሉ። አቃቢ ሕግ ኩም ብሎ፣ ክሴን አንስቻለሁ ይላል። ግንቦት 26 ቀን 22007 ዓ.ም ፣ የቦሌ ምድብ ችሎት ፍርድ ቤትም አቶ ማሙሸት እንዲለቀቁ ያዛል።
አቶ ማሙሸት መረጃ ስለነበራቸው ፖሊስ ክሱን ለማንሳት ተገደደ እንጂ፣ ሌሎች በሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ወያኔዎች እያሰሩ የሚያሰቃዩት ጥፋት ወይንም ወንጀል ሰርተው ሳይሆን በዉሸትና በፈጠራ እንደሆነ ይህ አንድ ትልቅ ማሳያ ነው።
አቶ ማሙሸት ፍርድ ቤቱን አመስግነው ወደ ቤታቸው ሊያቀኑ ሲሉ፣ ፖሊስ እንደገና አስሮ ይሄን ጊዜ ከማእከላዊ ቀጥሎ በቶርቸር ወደ ሚታወቀው የሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ይወስዳቸዋል። ስዬ አብርሃን ብርቱካን ሚደቅሳ ነጻ ስትለቀው፣ ከፍርድ ቤት ደጃፍ አንድ እርማጃ ሳይራመድ እንደገና ፖሊስ ይዞት እንዳሰረው ማለት ነው። ያኔ ስዬን የፈታችሁ ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ነበረች። አሁንም አቶ አማረ እንዲለቀቁ የወሰንነችዉም ዳኛ ብርቱካን ነው የምትባለው። ሴቶች ዳኛዎች ጀግኖች ናቸው እንበል !!! በመጽሀፍ ቅዱስ እንዳለችው ዲቦራ።
“ሚያዚያ 14 ቀን ሳይሆን ሚያዚያ 12 ቀን ነው ወጣቶችን አደራጅቶ ብጥበጣ የፈጠረ” የሚል ሌላ ክስ አቶ ማሙሸት ላይ ይመሰረትባቸዋል። ሰኔ 10 ቀን የአራዳ ችሎት ፍርድ ቤት፣ 5000 ብር ዋስትና ከፍለው ዉጭ ሆነው እንዲከራከሩ ትእዛዝ ይሰጣል። ዋስትና ተከፍሎ ወደ ቤታቸው ለመሄድ አቶ ማሙሸት ይዘጋጃሉ። ሆኖም ፖሊስ የፍርድ ቤት ትእዛዝ አልቀበልም ይላል።
በአገራች ፍርድ ቤቶች ያሉ ዳኞች፣ አብዛኞቹ ካድሬዎችና ለሙያቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ያደሩ ፣ ፍርድ የሚያዛቡና የሚያጣምሙ መሆናቸው ይታወቃል። ሆኖም አልፎ አልፎ ደግሞ ትንሽም ቢሆን፣ ኢንቴግሪቲ ያላቸው ዳኞች ሲገኙ፣ ፖሊስ እንደፈለገ የዳኞችን ዉሳኔ የሚሽርበት ሁኔታ ነው ያለው። ያን ያህል የፍርድ ስርዓቱ ፍጹም ጭቃ የሆነባት አገር ናት ኢትዮጵያ።
ፖሊስ ይግባኝ ብሎ ሰኔ 15 ቀን፣ አቶ ማሙሸትን ፍርድ ቤት ያቀርባል። “ቢለቀቅ ፣ የአቃቢ ሕግ ምስክሮችን ያጠፋብናል። የተከሰሰበት ወንጀል ከባድና ውቅታዊ ነው” በሚል የዋስታና መብት አቶ ማሙሸት እንዲከለከሉ ይጠይቃል። ካድሬ ዳኛውም የፖሊስን ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር ተቀብሎ፣ ፖሊስ ምርመራዉን እንዲጨርስ የ14 ቀናት ቀጠሮ ይሰጣል።
የአገሪቷ ሕግ መንግስት የዜጎችን የዋስትና መብት ያረጋግጣል። ግን ካድሬ ዳኞች ሕገ መንግስቱን አንብበው ሳይሆን ዉሳኔ የሚያስተላለፉት፣ በአቃቤ ሕግ በኩል ሕወሃቶች የሚልኩላቸውን የፖለቲካ ዉሳኔዎች ነው የሚያነቡት።
የአገሪቷ ሕግ መንግስት የዜጎችን የዋስትና መብት ያረጋግጣል። ግን ካድሬ ዳኞች ሕገ መንግስቱን አንብበው ሳይሆን ዉሳኔ የሚያስተላለፉት፣ በአቃቤ ሕግ በኩል ሕወሃቶች የሚልኩላቸውን የፖለቲካ ዉሳኔዎች ነው የሚያነቡት።
“የመጀመሪያውን ክስ ፍርድ ቤት በፃፈው ደብዳቤ ውድቅ ሆኗል፡፡ አሁን ደግሞ ዳኛዋ እንድለቀቅ ወስነዋል፡፡ ሆኖም ግን ፖሊስ እኔን መፍታት አልፈለገም፡፡ አሁንም ድረስ ታስሬ የምገኘው ባልዋልኩበት ነው፡፡ የታሰርኩት ባልሰራሁት ወንጀል ነው፡፡ እንግዲህ ቀጥሎ የሚመጣውን የምናየው ይሆናል፡፡ ምን እንደሚያደርጉ አላውቅም” ይላሉ አቶ ማሙሸት እየደረሰባቸው ስላለው ግፍፍ ሲናገሩ። እንደ ዜጋ ፍርድ ቤት መብታቸውን ሊያስጠብቅላቸው አልቻለም። እንደ ዜጋ ፍትህ ለማግኘት አልቻሉም። እነ ጌታቸው አሰፋ (የሕወሃት የደህንነት ሃላፊው) “ማሙሸት በወህኒ ይቆይ” የሚል ቀጭን ትእዛዝ ስለሰጠ ብቻ ፣ አቶ ማሙሸት በአሁኑ ጊዜ በወህኒ እየተሰቃዩ ይገኛሉ።
ዜጎች በአገራቸው በሰላም መኖር ካልቻሉ፤ በአገራቸው የሕግ ከለላ ካለገኙ፣ ጥቂቶች እንደፈለጉ ሕግ መንግስቱን ገልብጠው መንግስታዊ ሽብርና ዉንብድናን የሚፈጽሙ ከሆነ፣ እነርሱ ራሳቸው በጠራራ ጸሃይ ያፈረሱትን እና የናዱት፣ የረጋገጡትን ሕግ የመቀበልና የማክበር ግዴታ ሌሎች ሊኖራቸው አይችልም። አሁን ያለው የወያኔ ዘረኛ የናዚ ስርዓት የሕግ ጠላት እንጂ ፣ ሕግን አክባሪ አይደለም። ሕዝብን እያገለገ ሳይሆን፣ በሕዝብ ስም የሚገኝ እርዳታን እየመዘበረ፣ ጥቂት ፎቆችን ለይስሙላ እያሳየ ደጋፊዎችን ሃብታም እያደረገ፣ የኑሮ ዉድነቱን ከቁጥጥር ዉጭ ሆኖ አብዛኛውን ኢትዮጵያዊ በከፍተኛ ድህነት ዉስጥ የቀበረ፣ ዜጎችን እያሸበረ ያለ አሸባሪ ቡድን ነው።

(አቶ ማሙሸት በዋስትና እንዲለቀቁ የታዘዘበት ወረቀት ተያይዟል)
No comments:
Post a Comment