ጎንደር ውጥረት ላይ ነች
የጎንደር ሕዝብ ካልደፈረሰ አይጥራም ማለት በሕወሓት ጁንታ የሚደረግበትን ጭቆና መከፋፈል እና የመስፋፋት ፖሊሲ በመቃወት ታጥቆ መነሳቱ ሲታወቅ ሕዝብን በመበደል የሚታወቅ አንድ የሚሊሻ ሃላፊ በጎንደር ቀበሌ 15 ውስጥ ሕዝቡ እርምጃ እንደወሰደበት የታወቀ ሲሆን በአብጅራ እና አብድራፊ ጨምሮ በላይኛው እና ታችኛው አርማቾ እንዲሁም በአከባቢው ከፍተኛ ፍተሻ እየተደረገ ሲሆን የወልቃይት ጠገዴ ገበሬዎች በመሰብሰብ ተቃውሞ እያሰሙ እና የመስፋፋት ድርጊቱን እያወገዙ ያሉበት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ::የጎንደር ሕዝብ በፍጹም ከተነሳበት የነጻነት ትግል ወደ ኋላ እንደማይል በተግባር እያሳየ መሆኑ ተነግሯል::
No comments:
Post a Comment