Wednesday, March 18, 2015

በሀሰት አልመሰክርም በማለት አውነቱን በፍርድ ቤት የተናገረው ሙጂብ አሚኑ ለሚያዚያ 7 ተቀጠረ -

ርድ ቤት በርካቢቢኤን መጋቢት 9/2007 በነ ኤልያስ ከድር መዝገብ በተከከሰሱ ሙስሊሞች ላይ በሀሰት እንዲመሰክር ታፍኖ ማእከላዊ የተወሰደው ሙጂብ አሚኑ በሀሰት እንዲሰክር አቅርበውት አስገራሚ ታሪክ ሰርትዋል፡፡ በወንድሞቼ ላይ በሀሰት አልመሰክርም በማለት እውነቱን በፍርድ ቤት አስረድትዋል፡፡ ለዚህ እኩይ አላማቸው ማስፈጸሚያ አልሆንም ያለው ሙጂብ አሚኑ በሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶበት በማእከላዊ ይገኛል፡፡ በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርቦ የነበረ ሲሆን ለሚያዚያ 7 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ መንግስት የሰራው አይን ያወጣ ሸፍጥ ሁሉንም ያስገረመ ሲሆን ወጣት ሙጂብ አሚኑ የሚመጣውን ሁሉ ዋጋ ለመክፍል በመቁረጡ፤ እውነትን በመጋፈጡ በበርካቶች አድናቆትን ተችሮታል፡፡ ሙስሊሞች ለሱ ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት በዛሬው እለት በፍቶች ተገኝተዋል፡፡

No comments:

Post a Comment