
ከፍኖተ ሰላም ከተማ በስተምስራቅ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ጅጋ ከተማ ሕዝቡ ባነሳው ተቃውሞ የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች በተኮስቱት ጥይት 4 ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ ሕዝብ በወሰደው እርምጃ 3 ወታደሮች መሞታቸውም የአይን እማኞች ገልጸዋል::
የአካባቢው ሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲተኩስ ወደነበረ አንድ ፖሊስ መኖሪያ ቤት በመሄድም ንብረቱን አደባባይ በመዘርገፍ እንዳቃጠሉበት የተነገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሕዝብ ጎማዎችን በማቃጠል ከፍተኛውን ተቃውሞ እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል:: በተለይም የስር ዓቱ ደጋፊዎች ንብረት ነው የተባለ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስም በድንጋይ ተወግሮ መስታወቱ ከጥቅም ውጭ መሆኑ በፎቶ ጭምር የተለቀቀው መረጃ አሳይቷል::
የአካባቢው ሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲተኩስ ወደነበረ አንድ ፖሊስ መኖሪያ ቤት በመሄድም ንብረቱን አደባባይ በመዘርገፍ እንዳቃጠሉበት የተነገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሕዝብ ጎማዎችን በማቃጠል ከፍተኛውን ተቃውሞ እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል:: በተለይም የስር ዓቱ ደጋፊዎች ንብረት ነው የተባለ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስም በድንጋይ ተወግሮ መስታወቱ ከጥቅም ውጭ መሆኑ በፎቶ ጭምር የተለቀቀው መረጃ አሳይቷል::
No comments:
Post a Comment