Friday, August 26, 2016

በጎጃም ጅጋ ከተማ በተቀሰቀሰ አመጽ ከሕዝቡ 4 ከትግራይ ነጻ አውጪ ሰራዊት 3 ወታደሮች ተገደሉ

Jiga gojam(ዘ-ሐበሻ) በጎጃም ክፍለ ሃገር ጅጋ ከተማ ውስጥ የሃይማኖት አባቶች ሕዝቡን ለመገዘትና በመንግስት ላይ ያለውን የ እኩልነት ጥያቄ እንዲያቆሙ ለመጠየቅ የጠሩት ስብሰባ ወደ አመጽ ተሸጋግሮ በአሁኑ ወቅት ከተማዋ በክፍተኛ ተቃውሞ እየተናጠች መሆኑን ለዘ-ሐበሻ ከስፍራው የደረሱ መረጃዎች አመለከቱ::
ከፍኖተ ሰላም ከተማ በስተምስራቅ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ጅጋ ከተማ ሕዝቡ ባነሳው ተቃውሞ የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች በተኮስቱት ጥይት 4 ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ ሕዝብ በወሰደው እርምጃ 3 ወታደሮች መሞታቸውም የአይን እማኞች ገልጸዋል::
የአካባቢው ሕዝብ ወደ ሕዝብ ሲተኩስ ወደነበረ አንድ ፖሊስ መኖሪያ ቤት በመሄድም ንብረቱን አደባባይ በመዘርገፍ እንዳቃጠሉበት የተነገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሕዝብ ጎማዎችን በማቃጠል ከፍተኛውን ተቃውሞ እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል:: በተለይም የስር ዓቱ ደጋፊዎች ንብረት ነው የተባለ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስም በድንጋይ ተወግሮ መስታወቱ ከጥቅም ውጭ መሆኑ በፎቶ ጭምር የተለቀቀው መረጃ አሳይቷል::

No comments:

Post a Comment