Thursday, August 11, 2016

የጉራጌ ወጣቶች ለእሁድ ነሐሴ 15 በወልቂጤ እና ቡታጅራ ከተሞች ተቃውሞ ጠሩ

Bilderesultat for gurage ethiopia region“ለእሁድ ነሐሴ 15 የቡታጅራ እና ወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ተዘጋጁ” ይላል ለዘ-ሐበሻ የደረሰውና በጉራጌ ከተሞች እየተበነ ያለው ወረቀት:: “ላለፉት 25 ዓመታት በስልጣን ላይ ያለው የትግራይ መንግስት ቤተጉራጌን በማፈራረስና የጉራጌ ነጋዴን ከገበያ በማውጣት ያደረሰው በደል የተሰማችሁ ሁሉ እንዲሁም በኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ወንድም እና እህቶቻችሁ መገደል ያንገበግባችሁ እሁድ ነሐሴ 15 በወልቂጤና ቡታጅራ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት ተዘጋጁ” ይላል የተበተነው ወረቀት::

መንግስት በጉራጌ ማህበረሰብ ላይ የሚያደርሰውን በደል እና በሃገሪቱ ውስጥ እንደ እኩል ዜጋ ሳይቆጠር ከንግድ እንዲወጣ መደረጉ ያንገበገባቸው የጉራጌ ወጣቶች እሁድ ነሐሴ 15, 2016 በሚያድርጉት ተቃውሞ ላይ የተለያዩ ሃገራዊ መፈክሮችን ይዘው ይወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል::
በአዲስ አበባ በተለምዶ መርካቶ በሚባለው አካባቢ ድሮ የጉራጌ ነጋዴዎች ይበዙ የነበሩ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን ዙሩ ተገልብጦ የንግድ እድሉ በጠቅላላ ለትግራይ ተወላጆች ተሰጥቶ ጉራጌ ከመርካቶ ወጥቷል:: ቤተጉራጌም ሕወሓት በሚመራው መንግስት እንዲዳከም መደረጉ ይታወሳል::

No comments:

Post a Comment