Monday, June 15, 2015

የሕወሓት መንግስት የግንቦት 20ን በዓል በ20 ሰው በድብቅ በሚኒሶታ አከበረ

Girma biru(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት የሚኒሶታን ሕዝብ እንደ ጦር ነው የሚፈራው – ለዛም ነው ሕዝባዊ ስብሰባና በዓል ሲያደርግ በድብቅ የሚያደርገው:: ከዚህ ቀደም በአደባባይ ፖስተር ለጥፎ ስብሰባ ሲጠራ ሕዝቡ ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት በማወኩ ስብሰባው ሳይካሄድ ቀርቷል:: ትናንት June 13 በሚኒሶታ የሕወሓት መንግስት የግንቦት 20ን በዓል ለማክበር በሚኒሶታ በድብቅ ስብሰባ ጠርቶ ነበር:: በሚኒሶታ 5ለ1 በሚል ጥርነፋ የተደራጁ የሕወሓት መንግስት ደጋፊዎች ያሉ ሲሆን እነዚህ ሰዎች የየራሳቸውን ኮኔክሽን ቢጠሩም በስብሰባው ላይ ከ20 የበለጠ ሰው ሳይገኝ ቀርቷል:: በረመዳ ሆቴል በተደረገው በዚሁ በከሰረው የግንቦት 20 በዓል ላይ የሕወሓቱ ተላላኪና ከደንበል ሲቲ ሴንተር ጋር በተያያዘ በሙስና የሚታሙት አቶ ግርማ ብሩ የመጡ ቢሆንም በኪሳራ ወደመጡበት ተመልሰዋል:: ከአቶ ግርማ ብሩ የቀረቡ ምንጮች ባገኘነው መረጃ መሠረት በስብሰባው ላይ ከ20 ሰው በታች መገኘቱ በጣም ከመበሳጨታቸው የተነሳ በድብቅ የተጠሩት ሰዎች ሁሉ ባለመገኘታቸው “ምን አድርገናቸው ነው?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ነው:: የሕወሓት መንግስት በዓል የሆነው የግንቦት 20 በዓል በሚኒሶታ በባዶ አዳራሽ መካሄዱ ለሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ድል ነው:: - 

No comments:

Post a Comment