በአሁኑ ወቅት ጎግል ላይ ገብተው ኢትዮጵያ የሚል ቃል ቢጽፉ ከ100 በላይ ዜናዎችን በቅድሚያ የምታገኙት ስለአትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ነው:: ከ500 በላይ የኦሮሞ ተማሪዎች እና ከ200 በላይ አማሮች በዚህ በሰሞኑ የሕዝብ ተቃውሞ በሕወሓት መራሹ መንግስት ሲገደሉ ያላገኝነውን የዓለም አቀፍ ሚድያ መድረክ በአንድ ፈይሳ ሌሊሳ ተቃውሞ የዓለማችንን ታላላቅ ሚዲያዎችን ትኩረት አግኝተናል:: መለስ ዜናዊ ሲሞት ዜናውን ለ15 ሰከንድ የዘገበው የአሜሪካው ሲኤን ኤን ሳይቀር ለፈይሳ ሌሊሳ ተቃውሞና ያን አስታኮ ስለኢትዮጵያ ያለውን ግድያና የሰብአዊ መብት ረገጣ በሰፊው ዘግቧል::
የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ አትሌት ፈይሳ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ; ከተመለሰ በኋላም ስላደረገው ተቃውሞ ምንም የሚደርስበት ነገር የለም ማለታቸውን ተከትሎ ሬውተርስ የጀግናውን አትሌት ፈይሳ እናት የሆኑትን ወ/ሮ ብሪቱን አነጋግሯቸው ነበር::
ወይዘሮ ብሪቱ መንግስት ልጃቸውን ምንም አላደርገውም ወደሃገሩ ይግባ ያለውን ለሮይተርስ ምላሽ ሲሰጡ <ይሄ ነገር እናንተስ እውነት ይመስላችኋል?… እዛው ይቀመጥልኝ!> ሲሉ ተናግረዋል::
No comments:
Post a Comment