OPPOSITION PARTIES WEBSITES

ETHIO NEWS & VIEWS

RADIO & TV

Thursday, August 25, 2016

የአትሌት ፈይሳ ሌሊሳ እናት “መንግስት ያለውን አላምንም… ልጄ እዚያው ይቀመጥልኝ አሉ”

feysa lelisa mom በአሁኑ ወቅት ጎግል ላይ ገብተው ኢትዮጵያ የሚል ቃል ቢጽፉ ከ100 በላይ ዜናዎችን በቅድሚያ የምታገኙት ስለአትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ነው:: ከ500 በላይ የኦሮሞ ተማሪዎች እና ከ200 በላይ አማሮች በዚህ በሰሞኑ የሕዝብ ተቃውሞ በሕወሓት መራሹ መንግስት ሲገደሉ ያላገኝነውን የዓለም አቀፍ ሚድያ መድረክ በአንድ ፈይሳ ሌሊሳ ተቃውሞ የዓለማችንን ታላላቅ ሚዲያዎችን ትኩረት አግኝተናል:: መለስ ዜናዊ ሲሞት ዜናውን ለ15 ሰከንድ የዘገበው የአሜሪካው ሲኤን ኤን ሳይቀር ለፈይሳ ሌሊሳ ተቃውሞና ያን አስታኮ ስለኢትዮጵያ ያለውን ግድያና የሰብአዊ መብት ረገጣ በሰፊው ዘግቧል::
የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ አትሌት ፈይሳ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ; ከተመለሰ በኋላም ስላደረገው ተቃውሞ ምንም የሚደርስበት ነገር የለም ማለታቸውን ተከትሎ ሬውተርስ የጀግናውን አትሌት ፈይሳ እናት የሆኑትን ወ/ሮ ብሪቱን አነጋግሯቸው ነበር::
ወይዘሮ ብሪቱ መንግስት ልጃቸውን ምንም አላደርገውም ወደሃገሩ ይግባ ያለውን ለሮይተርስ ምላሽ ሲሰጡ <ይሄ ነገር እናንተስ እውነት ይመስላችኋል?… እዛው ይቀመጥልኝ!> ሲሉ ተናግረዋል::

No comments:

Post a Comment