

ሕወሓት በትግርኛ የሚያስተላልፋቸው መርዘኛ መልዕክቶቹ “አማራው ትግሬን ለማጥፋት ተነስቷል” የሚል ሲሆን አንዳንድ የትግራይ ተወላጆችም በዚህ መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ እየተታለሉ መሆኑ በግልጽ እየታየ ነው:: በተለይ በጎንደርም ሆነ በባህርዳር ዛሬም በደብረማርቆስ የወጣው ሰላማዊ ሰልፈኛ በትግራይ ነጻ አውጪ ሠራዊት ጥይት ሰለባ እየሆነ ሕዝቡ የሚናገረው “ጠላታችን ሕወሓት እንጂ የትግራይ ሕዝብ አይደለም” ቢልም ሕወሓት ግን ሆን ተብሎ የአማራው ሕዝብ የትግራይ ሕዝብን ሊያጠፋ ተነስቷል የሚል ፕሮፓጋዳ ሥራዎች ውስጥ መጠመዱ በይፋ ታይቷል::
በጎንደር ተቃውሞ ንብረታቸው በብዛት የወደመባቸው ለሕወሓት መንግስት ተላላኪ የሆኑ አማሮች ቢሆንም ሕወሓት ግን በትግርኛ ለትግራይ ሕዝብ የሚያስተላልፈው መረጃ የትግራይ ተወላጆች ንብረት ብቻ እንደወደመ ነው:: በዚህም መሰረት ሕዝብን ከሕዝብ ለማቃቃር ተግቶ የሚሰራው ሕወሓት ከጎንደር ትግራዮችን በአውሮፕላን እያስወጣ ፎቶዎችንም በሶሻል ሚድያዎች በመልቀቅ ለትግራይ ሕዝብ ቆሚያለው የሚል ፕሮፓጋንዳውን እየነዛ ነው::
በጎንደር ሰላማዊ ሰልፈኛው ማንኛውም ለ ስር ዓቱ እስካላቃጠረና ሕዝብን እስካላስጠቃ በሰላም መኖር ይችላል የሚል ጠንካራ መልዕት መስተላለፉ አይዘነጋም::
No comments:
Post a Comment