OPPOSITION PARTIES WEBSITES

ETHIO NEWS & VIEWS

RADIO & TV

Tuesday, April 28, 2015

ማሰር፣ ማሽበር፣ ማወክ የማይሰለቸው ግፈኛ አገዛዝ – ግርማ ካሳ


ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ማሻሻያዎች አድርጎ ለብሄርዊ መግባባት ራሱን እንዲያዘጋጅ ከተለያዩ ማእዘናት ጥሪ ቀርቦለታል። የሕሊና እስረኞችን እንዲፈታ በተደጋጋሚ ተጠይቋል። ሆኖም አገዛዙ እንኳን ሊሰማ እንደዉም በጣም እየባሰበት መጥቷል። ዜጎችን በማሰርና በማሸበር የሚረካው አገዛዝ ዛሬም በወገኖቻችን ላይ የሰቆቃ በትሩን እየያሳረፈ ነው።
በሊቢያ ለሚገኙ ወገኖቻችን አስቸኳይ ድጋፍና እርዳታ እንዲያደረግ እየተለመነ ያለው አገዛዙ ትኩርቱ ሕይወት ማዳን ላይ ሳይሆን በዜጎችን ላይ ስቃይ ማድረስ ሆኗል።
የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በፍቼ ሰልፍ ባደረገበት ወቅት በደህንነት አባላት ደም በደም እስኪሆን ድረስ የተደበደበውና የተሰባባረው መሳይ ምትኩ ፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ታማሚ ሆኖ በቤቱ ነበር የሚቀመጠው። «ከዚህ በፊት ተጎድቻለሁ፣ ትግሉ ይቅርብኝ» ሳይል ትግሉን ቀጠለ። ለምን አገሩን የሚወድ ነጻነትን የተጠማ በመሆኑ።
በቅርቡ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች እንደገና አፈኑት። በማእከላዊ ተወረወረ። በዚያ ቶርቸር እየተደረገ እንደሆነም መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በማእከላዊ እሥር ቤት በኤሌቲክ ገመድ ስይቀር እስረኞችን እንደሚገረፉ በቅርቡ የዞን ዘጠኙ ናትናኤል ፈለቀ ለጆን ኬሪ በጻፈው ደብዳቤ ገልጿል።
የረቡን ታሪካዊ ሰልፍ ተከትሎ ወይንሸት ሞላን ጨምሮ በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታስረዋል። ወይንሸት ሞላ ስትታሰር ይሄ ሶስተኛ ጊዜ መሆኑ ነው።
sntayehu
ዛሬ ደግሞ ወንድም ስንታየው ቸኮልን አፍነዉታል። ስንታየው ድብቅ ነገር አይወድም። ንግግሩ ቀጥተኛ ነው። ሐሳቡን የመሰለዉን ከመናገር ወደ ኋላ የማይል ነው። ሞትና መታሰርን በጭራሽ የማይፈራ ፣ አገሩን የሚወድ ጀግና ኢትዮጵያዊ ። እርሱ በመታፈኑ፣ በዜጎች ስቃይ የሚደሰቱ እንደመሆናቸው፣ አሳሪዎቹ ሊደሰቱ ይችሉ ይሆናል። በሺሆች የምንቆጠር የትግል አጋሮቹ ደግሞ ልናዝን እንችላለን። ከስንታየው ጋር ወዳጆች ነን። ስለ ስንታየሁ ብዙ አወቃለሁ። አንድ ነገር አስረግጬ የምናገረው ነገር ቢኖር፣ ስንታየው ለአገርና ለህዝብ ሲል መታሰርን እንደ ትልቅ ጸጋና ክብር የሚቆጠር፣ ወኔና ጀግንነት የተሞላ ኢትዮዮጵያ ካፈራቻቸው ብርቅዬ ታጋዮች መካከል አንዱ መሆኑን ነው።
ገዢው ፓርቲ ማስሩን ባጠናከረ ቁጥር በፖለቲክ መክሰሩን፣ በሐሳብ መሸነፉን፣ መዉደቂያው መቃረቡን እያመላከተ ነው። ተስፋ እየቆረጠ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስንታየው ቸኮሎች፣ ወይንሸት ሞላዎች፣ መሳይ ምትኩዎች አሏት። «ታጋይ ቢሞት ትግል አይሞትም» ነበር የሚባለው። ታጋይ ቢታሰርም ትግል አይታሰርም። ብርቱካን ሚደቅሳን አሰሩ፤ እነ አንዱዋለምን፣ እነ ርዮት አለሙን ተነሱ ። እነ አንዱዋለምን ሲታሰሩ እነ ሃብታሙ ፣ ዞን ዘጠኞች ተነሱ። እነ ሃብታሙ ሲታሰሩ ደግሞ እነ መሳይ ምትኩ እነ ስንታየሁ ተነሱ። የሕዝብ መሰረታዊ የለዉጥ ጥያቄን በኃይል ማፈን በጭራሽ አይቻልም።

No comments:

Post a Comment