
ከዚህም ባሻገር ‹‹አዋሳ ውስጥ መቀስቀስ አትችሉም፡፡ ከተማውን ለቃችሁ ውጡ፡፡ ለቃችሁ ካልወጣችሁ መኪናውን ለ10 ቀን እናስረዋለን፡፡ 10 ሺህ ብርም እንቀጣችኋለን›› እያሉ የመኪናውን ባለቤትና ቀስቃሾቹን እያዋከቡ እንደሚገኙ የቅስቀሳው ተሳታፊዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ደህንነቶች፣ ፖሊሶችና ካድሬዎች እያደረጉት ባለው ወከባም የመኪና ላይ ቅስቀሳው ለጊዜው እንደተቋረጠ ለማወቅ ተችሏል፡፡
No comments:
Post a Comment